Jul 2024

የግድቤን በደጀ (የጣሪያ ላይ የዝናብ ውሃ ማሰባሠብ ፐሮጀክት )ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ።

''የግድቤን በደጀ'' ትግበራ ከዚህ በፊት ውሃ ለመያዝ የተሞከረውን አሰራር በማሻሻልና በቴክኖሎጅ የተደገፈ በማድረግ እየተተገበረ የሚገኝ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ ትልቅ መዋእለ ንዋይ የሚጠይቅን የውሃ ፕሮጀክት በቀላል ወጭ ተገንብቶ በተለይም ውሃ አጠር የሆኑ አካባቢዎችን ትልቅ መፍትሄ ለመስጠት ያግዛል ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የመጠጥ ውሃና የኢነርጅ ፕሮጀክቶችን ለማየት ድሬዳዋ ገቡ።

ክቡር ሚኒስትሩ በቆይታቸው የግድቤን በደጀ ፕሮጀክቶችንና የኢነርጅ ፕሮጀክቶቾን የሚጎበኙና የሚያስመርቁ ይሆናል። በጉብኝቱ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊን ጨምሮ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች ተሳታፊ ናቸው።

የአየር ንብረት ለውጥ እና የዘላቂ የልማት እቅድ የሚያቀናጅ የንፁህ የምግብ ማብሳያ ፍኖታ ካርታ ዝግጅት ላይ ምክክር እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒሰቴር የብሔራዊ ባዮጋዝ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመሰገን ተፈራ በሀገራችን የመስኖ እና ግብርና ሴክተሮች ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ መሆናቸውን ገልፀው፤ አርብቶ አደሮች እና በዝናብ ላይ በተመሰረተ ግብርና ላይ ጥገኛ የሆኑ አነስተኛ ይዞታ ያላቸው አርሶ አደሮች ደግሞ ለአየር ንብረት ለውጥ

2016ዓ.ም የበጀት አመት በችግሮች ውስጥ ሆኖ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ያሳየንበት የስራ ዘመን ነበር።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ በሀገራችን የተቀመጡ የልማት ግቦችን ለማሳካት ከተቀመጡ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ዘርፎች ውስጥ ውሃና ኢነርጂ አንዱ ዘርፍ መሆኑን ጠቅሰው የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀምን ከማሻሻል፣ የመጠጥ ውሃ ና ሳኒቴሽን አቅርቦት ተደራሽነትን ከማረጋገጥ እንዲሁም አገራዊ የኢነርጂ አቅር

የባለብዙ ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በውሃ ኢነርጂ ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዘላቂነት በሚገባ መፈተሽና ማረጋገጥ እንደሚገባ እና እንደ ''ግድቤን በደጄ'' አይነት በግለሰብ ደረጃ ሊሰሩ የሚችሉ የውሃ አቅርቦት ስራዎች በልዩ ትኩረት እንደሚተገበሩ ገልጸዋል።

እየተካሄደ በሚገኘው አመታዊ የባለብዙ ባለድርሻ አካላት ፎረም የኢነርጂ ልማት ዘርፍ በልዩ ልዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል።

በፎረሙ ላይ የኤሌክትርፍኬሽን ጥናት፣ በአደሌ ፕሮጀክት አተገባበር፣ ፕራይም ፕሮጀክት 1፣ ኢነርጂ ሴክተር ሪፎርምን በተመለከተ፣ ኢንቨስትመንት፣ ማዘመን የመሳሰሉት ላይ፤ እንዲሁም ክላይሜት ፕሮሚስ ፕሮጀክት1 ዙሪያ ትኩረት ያደረጉ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

እየተካሄደ በሚገኘው አመታዊ የባለብዙ ባለድርሻ አካላት ፎረም በመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ዘርፍ በልዩ ልዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል።

የፋይናንስ ስትራተጂው አላማ ዘላቂ የፋይናንስ ስትራተጂ ስርዓት በመዘርጋት ውጤታማ የዋሽ አፈጻጸም ማምጣት እንደሚቻል ተገልጿል። የፋይናንስ ስትራተጂው ተግባራዊ መደረጉ የሀገር ውስጥ ፋይናንስ ማሰባሰብና ማንቀሳቀስ ፣ ነባር የዋሽ ኢንቨስትመንት ማሻሻል ፣ የግል አክተሮች እና የፋይናንስ ተቋማት በዘርፉ ላይ ንዋይ መዋ

እየተካሄደ በሚገኘው አመታዊ የባለብዙ ባለድርሻ አካላት ፎረም በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ በልዩ ልዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል።

በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም እና ፕሮጀክት ላይ፤ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮጀክት ትግበራ የሀብት ማፈላለግ ስራዎችን በተመከለተ፤ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮጀክት ሂደትና ለውጥን በተመለከተ፤ ድንበር ተሸጋሪ የውሃ ሀብት አስተዳደር ላይ በተለይ፣ ቀጠናዊ

ዜጎችን በመጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ በኢነርጂ ተደራሽ ለማድረግ እና ጽዱ ሀገርንና አካባቢን ለመፍጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ትብብርና ተሳትፎ ወሳኝ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እያደገ የመጣውን ልማት በመደገፍ እና በተግዳሮት ፊት በመጽናት ፍትሃዊ እና ዘላቂ የውሃና ኢነርጂ ልማት ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዩኢንዲፒ ጋር በመተባበር በኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አምራች ሴቶች ስልጠና እየሰጠ ነው።

የዩኤንዲ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ስልጠናው በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ እና የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ማምረት ላይ ተሰማርተው እየሰሩ ላሉ ከ75 ሴቶች በላይ ለሆኑ ስራ ፈጣሪዎች የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፤ ሰልጣኖቹ በተሰማሩበት መስክ በቂ እውቀት እንዲያገኙና ውጤታማ እንዲሆኑ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

ከመጠጥ ውሃ ጋር ተያይዞ የሚታዩ የዲዛይን ጥራት ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና ተሠጠ።

የክቡር ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ እንደሀገር የዲዛይን ጥራት ችግሮች እንደሚስተዋሉ ጠቅሰው እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የቲወሪ ስልጠናዎች ብቻ በቂ ባለመሆናቸው እንደዚህ አይነት ተግባራዊ የአቅም ግንባታ ስልጠናወች እንደ ሀገር የተሟላ ስራ ለመስራት ያግዛሉ ብለዋል።

የኢነርጂ ሴክተር ሪፎርምና የፕራይም ፕሮጀክት አንድ(PRIME project 1)ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ ጎሳየ መንግስቴ የሀይል ዘርፍ ማሻሻያን የተመለከተ ጽሁፍ የኢትዮጵያ የሀይል ስርዓት እቅድ ማእቀፍ ስራን ከተቋም አንጻር በመገምገም ለመቆጣጠር መግባባት ላይ መደረሱ እና የመንግስትና የግል ሴክተሮች በዘርፉ ያላቸውን ሚና አስመልክቶ በእቅድ መካተቱን አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ ከኩባ መንግስት ጋር በውሃ ሀብት ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመች፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ እና የኩባ ብሔራዊ ሀይድሮሊክስ ኢንስቲትዩት ምክትል ፕሬዝዳንት ዣቪየር ቶሌዶ መካከል የተፈረመው ስምምነት የውሃ ሀብት አስተዳደር፣ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አቅርቦት፣ የረጅምና የአጭር ጊዜ የአቅም ግንባታ ስልጠና፣ በምርምር እና ስርጸት፣ በሚቲዮሮሎጂ አየር ትንብያ ሂደት፣ የመረጃ አሰ

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ከወተር ኤድ ጋር በመተባበር የአቅም ግንባታ ማሰልጠኛ እና የማስተማሪያ ሞጁሎችን አዘጋጀ፡፡

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ በብሔራዊ ደረጃ የዋሽ አቅም ግንባታ የማሰልጠኛ እና የማስተማሪያ ሞጁሎች መዘጋጀታቸየው ለውሃው ዘርፍ አቅም ግንባታ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸው፤ በውሃ ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች በአግባቡ እንዲጠቀሙበት ጠይቀዋል፡፡

እስከ 3000 አባዉራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ባለ270 ኪሎ ዋት የሶላር ሀይል ማመንጫ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በቦታው ተገኝተው የሀይል ማመንጫውን ባስመረቁበት ወቅት ባስተላለፉት መልእክት ፕሮጀክቱ ከዋና የሀይል መስመር ውጭ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሚተገበሩ የታዳሽ ሀይል አቅርቦት ስራዎች መካከል መሆኑን አንስተው፣ ፕሮጀክቱ ለመብራት፣ ለማብሰያ፣ ለጤና ተቋማት፣ ለትምህ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአፋር ክልል ዞን ሶስት በ4 ወረዳዎች የቅድመ ጎርፍ መከላከል ስራዎችን አስጀመረ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በየአመቱ የጎርፍ መከላከል ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው፤ የሚቲዎሮሎጂ ትንበያን መሰረት በማድረግ ከአለም ባንክ በተገኘ ድጋፍ በአጭር ጊዜ ህብረተሰቡን ለመታደግ የሚያስችል ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል።

የላይኛው አዋሽ ተፋሰስ የቅድመ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በጎርፍ ምክንያት የሚደርሰውን አደጋ ስጋቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ከአለም ባንክ በተገኘ የ300 ሚልዮን ዶላር ድጋፍ የኢትዮጵያ የጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት ተቀርጾ ዝግጅት ሲካሄድ መቆየቱን ገልጸው፤ በአየር ንብረት ለውጥ ትንበያ መሠረት ከመደበኛና ከመደበኛ በላይ በክረምት ዝናብ ምክንያ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአፋር ክልል በታችኛው አዋሽ የጎርፍ መከላከል ስራ አስጀመረ።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ይህ የአጭር ጊዜ የጎርፍ መከላከል ስራ በአለም ባንክ ድጋፍ የሚተገበረው የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት አካል መሆኑን ገልጸው፤ በ512 ሚሊየን ብር የአስቸኳይ የቅድመጎርፍ መከላከል ስራ በመስራት ህብረተሰቡን ከጉዳት መታደግ ታሳቢ መደረጉን ተናግረዋል።

እስከ 300 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ አነስተኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ በሀድያ ዞን በግቤ ወረዳ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ፕሮጀክቱ እስከ 300 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀው፤ ፕሮጀክቱ ከዋና የሀይል መስመር ውጪ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሀገር ከተያዙት እቅድ መካከል መሆኑን ተናረዋል፡፡

Jun 2024

የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች ''ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር ነፃነት እና ሉአላዊነት'' በሚል በተዘጋጀው አገራዊ ሰነድ ላይ ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሆነ የከርሰምድርና የገጸምድር ሀብት አቅም ቢኖራትም በአግባቡ መጠቀም አልቻልንም ይህም በድህነት፣ በብድር፣ በልመና አስተሳሰብ እንድንወድቅ አድርጎናል፤ ብድር በአገር ላይ ፓለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናን በመፍጠር ሙስና እንዲስፋፋ ያደርጋል በመሆኑም ከዚህ አስ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በ412 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ የግንባታና የማማከር ውል ስምምነት ተፈራረመ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሀ ፕሮጀክት በአለም ባንክ ገንዘብ ድጋፍ በ55 ወረዳዎች 110 ቀበሌዎች በድንበር አካባቢዎች በተደጋጋሚ ድርቅ በሚከሰትባቸው እና ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች እየተተገበሩ ላሉና ተግባራዊ ለሚደረጉ ፕሮጀክቶች በግንባታና በማማከር ስራ ውል መገባቱን

ከ515 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የቅድመ ጎርፍ መከላከል የሲቪል ስራዎችን ለማከናወን የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የቅድመ ጎርፍ መከላከል ስራው የአጭር ጊዜ መፍትሄ ለመስጠት የሚሰራ በመሆኑ ከሚገኘው ትርፍ በላቀ ማህበረሰቡን ከአደጋ መታደግ ትልቁ ትርፍ መሆኑን ተረድታችሁ በተቀመጠው አጭር ጊዜ ስራውን በማከናወን ትልቅ ማህበራዊ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ሲሉ ለኮንትራክተሮቹ አደራ ሰጥተዋል፡፡

በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በሙህር አክሊል ወረዳ የመጠጥ ውሃ ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የወረዳው የዘመናት ጥያቄ የሆነውን የመቆርቆር የውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙትን በማመስገን ለሠው ልጅ አስፈላጊና ህይወት የሆነን የውሃ ሀብት መጠበቅ፣ መንከባከብና ማልማት ተገቢ መሆኑን ጠቁመው

የጣና ንኡስ ተፋሰስ እቅድን ወደ ትግበራ ለማስገባት ከባለድርሻና አጋር አካላት ጋር ምክክር ተደረገ፡፡

በምክክር መድረኩ የአባይ ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የወንድወሰን መንግስቱ የተፋሰስ እቅዱን በሚገባ መተግበር በቤዚኑ የሚታዩ በርካታ ችግሮችን በመፍታት ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤

የአየር ንብረት ለውጥ በውሃ አቅርቦት ፣ሳኒቴሽንና ኢነርጅ ልማቶች ላይ የሚያስከትለውን ተጽእኖ ለመከላከል እና ለመቀነስ የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ አለማችን እየገጠማት ካለው ችግር አንዱና ዋነኛው የአየር ንብረት ለውጥ በፍጥነት መከሰት መሆኑን ጠቁመው ሀገራችንም ለዚህ ችግር ተጋላጭ ከሆኑ ሀገሮች አንዷ ናት ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 110 ሞተር ሳይክሎችን ለክልሎች አከፋፈለ።

ሞተር ሳይክሎቹ የኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሀ ፕሮጀክት ፕሮግራም በተደጋጋሚ ድርቅ በሚያጠቃቸው አካባቢዎች እየተተገበሩ ላሉ መካከለኛ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የክልሎችን አቅም ለማጠናከርና በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተገዙ መሆናቸውን ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ተናግረዋል፡፡

“በድንበርና ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብቶቻችን ብሔራዊ ጥቅማችንን እናሳድግ” በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ስለየውሃ ሀብቶቻችን ሊኖረን የሚገባውን ግንዛቤና እውቀት ማሳደግ አስፈላጊ በመሆኑ፤ መድረኩ በውሃ ሀብቶቻችን አጠቃቀም ዙሪያ ፍትሀዊነት የማረጋገጥ ስራ ለመስራት፣ የሀገራችንን የልማት ፍላጎት እንዲሁም ብሔራዊ ጥቅማችን እንዲከበር ጉልህ አስተዋጽኦ እንደ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአለታ ወንዶ ከተማ አስተዳደር ጋር የ308.5 ሚሊዮን ብር የብድር ስምምነት ተፈራረመ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በአለታ ወንዶ ለረጅም ጊዜ የነበረውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመፍታት የሚያስችልና ከከተማው መስፋፋት ጋር ተያይዞ የንግድ እንቅስቃሴ የሚስተዋልበት በመሆኑ ግንባታው የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግርን የሚፈታ ነው ብለዋል፡፡

“የመገናኛ ብዙሀን እና የህዝብ ግንኙነት ሚና ለታላቁ ህዳሴ ግድብ” በሚል ርእስ የምክክር ፎረም ተካሄደ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የህዳሴ ግድብ ሲገነባ ሚዲያ ዋነኛ ሚናውን መጨወቱን አነስተው፤ ወቅታዊ መረጃዎችን በማድረስ ህዛባዊ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ አስችለዋል ብለዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት የ100 ቀናት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።

የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ መንገሻ ሪፖርቱ እንደ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በበጀት አመቱ የነበሩንን ጠንካራ ጎኖች በማጎልበት፣ በአፈፃፀም ወቅት የነበሩትን ክፍተትቶች በማሻሻል ለቀጣይ 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በውሃ ሀብት አስተዳደር ፣ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እንዲሁም በኢነርጂ ልማት

አባያ እና ዝዋይ/ደንበል ሀይቆች የእምቦጭ አረም አወጋገድ ስራ ግምገማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተካሄደ።

የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ዴቢሶ ዴዴ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት የገለጹ ሲሆን፤ መንግስት ይህንን አረም ለማስወገድ ቁርጠኛ አቋም በመውሰድ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መቆየቱን እና በቀጣይም ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

The 3rd AFRI-RUN is underway.

H.E. Dr. Ing. Sultan Wali, State Minister for Energy Development sector at the Ministry of Water and Energy underscored the development unfolding with regard to cooperation endeavors among riparian co

2ኛ ዙር የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ተጨማሪ ብድር በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸደቀ፡፡

በ35ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ከተላለፉ ውሳኔዎች መካከል የኢትዮጵያ መንግስት ከዓለም አቀፍ የልማት ማህበር ጋር የ2ኛ ዙር የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ተጨማሪ ብድር ለማግኘት የተፈረመውን የብድር ስምምነት ማጽደቅ ይገኝበታል፡፡

በወላይታ ዞን ሆቢቻ ወረዳ 15ሺ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሀ ተጠቃሚ የሚያደርግ መካከለኛ የመጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

የመጠጥ ውሀና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሀ ፕሮጀክት በተለያዩ ክልሎች መጀመራቸውን ገልጸው፤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ሆቢቾ ወረዳ የዚሁ ፕሮጀክት አካል መሆኑን ተናግረዋል።

የደምበል ሻላ ንዑስ ተፋሰስ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ አስማማው ቁሜ እንደገለፁት ቀደም ብሎ በስምጥ ሸለቆ ቤዚን የተጀመረውን የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ሥራዎችን በደምበል ሻላ ንዑስ ተፋሰስ እቅድ አተገባበር ዙሪያ በማስፋት በቀጣይ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

እ.ኤ.አ ከጁን 11 እስከ 20/2024 የሚኖረው የአየር ሁኔታ አዝማሚያ በውሀው ዘርፍ ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ

በሚቀጥሉት ቀናት በአባይ፣ በላይኛውና በመካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አዋሽ እና ተከዜ እንዲሁም በጥቂት የአፋር ደናክል ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የእርጥበት ሁኔታን ያገኛሉ፡

እ.ኤ.አ ከጁን 11 እስከ 20/2024 የሚኖረው የአየር ሁኔታ አዝማሚያ በእርሻ ሥራ ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅዕኖ

በሚቀጥሉት ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት የበልግ እርጥበት ተጠቃሚ በሆኑት የሀገሪቱ አካባቢዎች ዘግይተው ለተዘሩ እና ፍሬ በመሙላት ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች፣ ለቋሚ ተክሎች፣ ለጓሮ አትክልቶችና ፍራፍሬዎች የውሃ ፍላጎትን ከማሟላት አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

እ.ኤ.አ ጁን 21 እስከ 30/2024 የሚኖረው የአየር ሁኔታ

በመጪው የጁን ሶስተኛው አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ክስተቶች ከመጠናከራቸው ጋር ተያይዞ በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብና በመካከለኛዉ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የደመና ክምችት ይኖራቸዋል፡፡

የተፋሰስ እቅድ የውሃ ሀብታችን ለማልማት፣ ለማስተዳደርና በፍትሃዊነት ለመጠቀም የሚያስችል ቁልፍ መሳሪያ ነው፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የውሃ ሀብቱን በማልማት እና በማስተዳደር በፍትሃዊነት ለመጠቀም እቅድ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን ጠቅሰው እንደሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውሃን ማዕከል ተደርጎ ሲሰራ የኢነርጂ ልማትን ለማስፋፋት፣ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ለማዋል፣ ማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማደረግ ፣ እንዲሁም ያ

በሲዳማ ክልል በደቡባዊ ዞን ዳራ ወረዳ አዳሜ ቴሶ እና ቁማጦ ቀበሌ መካከለኛ የመጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አሁን ላይ እየተለወጠ የመጣው ስራ ሳናስጀምር የመሠረት ድንጋይ አናስቀምጥም፤ ይህ ደግሞ ብልጽግና የሚለይበት ነው በማለት ንግግራቸውን የጀመሩት ክቡር ሚኒስትሩ፤ በሀገራችን እየመጣ ያለውን ለውጥ በተጨባጭ እያየን ነው ብለዋል፤ እንደማሳያም የመጠጥ ውሃ ሽፋንን ለማሳደግ የሚደረገው ጥረ

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በማስፈን ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ባለፉት 4እና 5አመታት ዝግጅት በማድረግ በተፉሰሱ ካሉ ክልሎች ፣ ባለድርሻ አካላት ፣ውሃን መሠረት አድርገው ከሚሠሩ አካላት እና በአጠቃላይ የተፋሰሱ ሀብት ተጠቃሚ የሆኑ አካላትን ጭምር በማሳተፍ የሶስቱ ቤዚን እቅድ የመጨረሻ ደረጃ መድረስ ችሏል ብለዋል።

በቦረና ዞን ጉቺ ወረዳ ኤርደር ቀበሌ መካከለኛ የመጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እና የመጠጥ ውሀና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በጋራ ሲሆን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሀ ፕሮጀክት ተግባራዊ ከሚያደርጋቸው አንዱ ሲሆን፤ በአንድ አመት ተጠናቆ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው

የቦረና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

በውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ልዑክ በቦረና ዞን የጉድጓድ መጥረግና የዉሃ ማጠራቀሚያ ግንባተ ስራው በአፍሪካ ልማት ባንክ ድጋፍ እንዲሁም በፌደራል መንግስት ድገፍ በCR wash እየተገነባ የሚገኘውን ፕሮጀክት በጎበኙበት ወቅት ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃለመጠይቅ የቦረና

ከ120 ሚሊየን ህዝብ በላይ ተጠቃሚ የሚያደርግ የተፋጠነ ዘላቂና ንጹህ የኢነርጂ ተደራሽነት ትራንስፎርሜሽን ፕሮግራም በዛምቢያ ሉሳካ ከተማ ይፋ ተደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የተመራ ልዑክ በዛምቢያ ሉሳካ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘውና ከ120 ሚሊየን ህዝብ በላይ በምስራቅና ደቡባዊ የአፍሪካ ቀጠና ያሉ ሃገራትን ተጠቃሚ በሚያደርገው የተፋጠነ ዘላቂና ንጹህ የኢነርጂ ተደራሽነት ትራንስፎርሜሽን (Accelerating Sustainable & Clean Energ

በቦረና ዞን ድሬና ዲዳያቤሎ ወረዳዎች መካከለኛ የመጠጥ ውሀ ፕሮጀክት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተጣለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ዛሬ በቦረና ዞን የተገኘነው በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሀ ፕሮጀክት በአለም ባንክ የሚደገፍ ፕሮጀክት ስራ ማስጀመሪያ ላይ ነው በማለት፤ ፕሮጀክቱ በድንበር አካባቢ ባሉ በተለይ ከአጎራባች አገሮች ጋር የሚዋሰኑና ከፍተኛ ድርቅ በየአመቱ የሚያጠቃቸው ወረዳዎችን በል

ከ168 ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የሚሌ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የሚሌ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ2012ዓ.ም ከአፋር ውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን ጋር ውል ተወስዶ ወደ ስራ የተገባ ቢሆንም በወቅቱ በነበረው የጸጥታ ችግር፣ የኮንስትራክሽኑ ስራውን ለማከናወን የአቅም ማነስና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት ፕሮጀክቱን ማጠናቀቅ አለመቻሉን አስታውሰው አሁን ላይ የ