Oct 2025

ለሶስት ክልሎች ለውሃ ተቋማት ግንባታና ጥገና አገልግሎት የሚውሉ የክሬን ማውንትድ ትራክ (Crain Mounted Truck) ድጋፍ ተደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ 5ቱን የክሬን ማውንትድ ትራክ (Crain Mounted Truck) ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ካንትሪ ተወካይ ከዶ/ር አቡባካር ካምፖ ተረክበው ዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር አንድ አካል በመሆን በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝና የውሃ ተቋማትን ለመጠገን፣ መልሶ ለማቋቋምና ሌ

በከርሰ ምድር የውሃ ጥራት ክትትል ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

በጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ በጋራ የተዘጋጀውና የከርሰ ምድር ውሃ ጥራትና ክትትል ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበረ ያለውን የተቀናጀ ውሃ ሀብት አስተዳደር ለማስፈን ከባዘር ኔት ፕሮጀክት ጋር በጋራ የሚደግፍ በመሆኑ በተለይ የከርሰ ምድር ውሃ ጥራትና ክትትል በማድረግ በማበልጸ

የባዘርኔት ፕሮጀክትን በውጤታማነት ለመተግበር የስትሪንግ እና ቴክኒክ ኮሚቴ ድርሻቸው የላቀ ነው ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የከርሰምድር ውሃ ሀብት የወንዝ ፍሰትና ጥራት በሙሉ የሚከናወኑት መሬት ላይ ነው:: በክልል፣ በዞንና ወረዳ ደረጃ ዝቅ ሲልም ቀበሌ ላይ የምንተገብራቸው ስራዎች ተደምረው ለሀገር በረከት ስለሚያመጡ ለፕሮጀክቱ ተግባራዊነት ቅንጅታዊ አሰራራችን አጠናክረን በመቀጠል የልማቱ ተቋዳሽ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከሶላር አቅራቢ ድርጅቶች ጋር መክረዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአለም ባንክ ባገኘው የ10 ሚሊየን ዶላር የብድር ድጋፍ በብርሃን ተደራሽነት ለሁሉም (ADELE) ፕሮጀክት ተግባራዊ ሲደረግ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማጠናከር ቀጣይነት ያለው የሶላር ስርጭት በአገሪቱ ገጠራማ አካባቢ ተደራሽ እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ መሆኑንም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አብራርተዋል።

በስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ኩልፎ ወንዝ ዙሪያ ለሚሰራው የጎርፍ መከላከል ተግባር የዓለም ባንክ ልዑካን ቡድን የመስክ ምልከታ አካሄደ

በፕሮጄክቱ የቴክኒካል ስራዎች፣ አከባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖን ከማረጋገጥ አንጻር የተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ከዕቅዱ አንጻር የተሰሩ ስራዎችን አስመልክቶ የዓለም ባንክ ልዑክ ቡድን መሪ ሱራብ ዳኒ (Surab Dani) የማሻሻያ ሀሳቦችን አንስተዋል። አክለዉም የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጄክት አስተባባሪ አቶ ተመ

ከ 215 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የ17 ፕሮጀክቶችን የመጠጥ ውሃ ጥናትና ዲዛን ከሚያከናውኑ አማካሪ ድርጅቶች ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት ድርቅ በሚያጠቃቸው አካባቢዎች አስቸኳይ መፍትሄ ለመስጠት 110 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት በታቀደው መሰረት የ22 ፕሮጀክቶች ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የተሻለና የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል ሪፎርም እንደሚያስፈልገው ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ የተሻለና የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ለማስቻል ሪፎርም እንደሚያስፈልገው ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሪፎርሙን ተከትሎ ባለፉት 4 አመታት በኢነርጂው ዘርፍ ብዙ ስራዎች ተሰርተው ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበችና ለጎረቤት ሀገራት ጭምር የኤሌክትሪክ ሀይል እያቀረበች እንደሆ

Sep 2025

የናይል ሀገራ ትብብር (Naile Basin Initative) የውሃ ጥራትን ለመለካት የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃ ጥራትና መጠን ልኬት ጉዳይ በተለይም በአውሮፓ ሀገራት ውስጥ በትኩረት የሚሰራበት መሆኑን ጠቅሰው ወደ ወንዝ የሚገባውም ሆነ የሚወጣው እያንዳንዱ ሊትር ውሃ ክትትል ሊደረግበት እንደሚገባና እስካሁን እንደሀገር በዚህ ደረጃ አለመሆናችንን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ ሀብ

የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከቻይና ህዝብ የፖለቲካ መማክርት ጉባኤ (CPPCC) ሉካን ቡድን አባላት ጋር ውይይት አደረገ።

ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንደገለፁት ቻይናና ኢትዮጲያ የሚያመሳስላቸው ሁለቱም ሀገራት ቀደምት የስልጣኔ መፍለቂያ የባህልና የቅርስ ባለቤት መሆናቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ቻይና ለኢትዮጲያ ሪፎርሙን በመደገፍ በተለያየ ዘርፍ ላይ ድጋፍና ትብብር እያደረገች መሆኑን ገልፅው በኢነርጂ ዘርፍም ለሚደረገው ትብብርና

ለአንድ ተቋም ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራርና መናበብ ወሳኝ እንደሆነ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለፈ ከክልሎች ጋር መቀናጀትና መናበብ እንደሚያስፈልግ አሳስበው፤ ቅንጅቱም በሀብት አጠቃቀም፣ በመረጃ አያያዝ፣ በመረጃ አቀራረብና ፍሰት መደበኛ ስራዎች ከፕሮጀክቶችና ከባድርሻ አካላት ጭምር መሆን እንዳበት ገለጸዋል፡፡

የሳኒቴሽን መሰረተ ልማቶችን በወቅቱና በጥራት አጠናቆ ለአገልግሎት መብቃት እንዳለባቸው ተጠቆመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ መድረኩን በመሩበት ወቅት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንደሌላው ፕሮጀክት ችላ የሚባልና ጊዜ የሚሰጠው ሳይሆን ትኩረት ሰጥተን ህብረሰሰባችንን የንፁህ መጠጥ ውሃ እና የሳኒቴሽን መሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ትኩረት ሊሰጠው ይገባልም ብለዋል።

የሴቶችን የአመራር ብቃት ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኦልቀባ ባሽ ሴቶችን ወደ አመራርነት ለማምጣት ማብቃት ያስፈልጋል፤ ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ 50 የተቋማችን ሴት አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ያሉባቸውን ክፍተቶች በመለየት የአመራር ብቃታቸውን ለማሳደግ ብሎም ወደ አመራርነት ለማምጣት አጋዥ የ

ከ219 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የማማከር ውል ስምምነት ተፈረመ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በ4 ክልሎች ማለትም በደቡብ ኢትዮጵያ ፣ በሶማሊ ክልል ፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ እንዲሁም በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ለሚያስገነባቸው 10 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ከ219 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከ ታርን አማካሪ፣ አዋሽ አማካሪ፤ ሚልኪ አማካሪና አሀዱ አማካሪዎች ጋር የውል ስምምነቶች

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት የ2017 ዓ.ም የክረምት ስራዎችን ገመገመ፡፡

ግምገማው በአዋሽ ፣ በስምጥ ሸለቆ ሀይቆች እና በኦሞ ጊቤ ወንዞች በ12ቱ ፕሮጀክቶች (12 lots) እየተተገበሩ ባሉ ስራዎች ላይ ያተኮረ ሲሆን ለውይይት መነሻ የሚሆን ጽሁፍ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኘሮጀክቱ የክትትልና ግምገማ አማካሪ በአቶ ተክሊት ብርሃነ የእያንዳንዱ የፊዝካል ስራዎች ፣ የፋይናንሻል አጠቃቀምና

የመረጃ አያያዝንና ልውውጥን ለማዘመንና ለማሳለጥ የሚያስችሉ የተለያዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ በርካታ ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው የቴክኖሎጂ መሳሪያዎቹ ዋና ዓላማቸው በተመረጡ 22 ከተሞች የውሃ አገልሎቶችን የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ለማዝመንና ለማሳለጥ በመሆኑ ተጠቃሚዎች ይህን ተገንዝበው ለታለመለት ዓላማ ብቻ በማዋል የዘርፉን

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ገሬኖ እንሰት ተክል ላይ እያስገነባው ያለውን የንፁህ መጠጥ ውሃን ምልከታ አደረጉ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ዶ/ር የተመራው ልዑክ በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ገሬኖ እንሰት ተክል ላይ Children Investement Fund Foundation(CIFF) እያስገነባው ያለውን የንፁህ መጠጥ ውሃን ምልከታ አደረጉ።

መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ 440 ቤተሰብ የበዓል መዋያ ድጋፍ ተደረገ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማይቻለው ተችሎ በብዙ ውጣ ውረድና ፈተናዎች ስትፈተን የቆየችውን የኢትዮጵያችን ማንሰራራት ጅማሮ በእጅጉ ያበሰርንበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ምርቃት ማግስት ይህንን ማዕድ ስናጋራ በእኔና በተቋሙ አመራሮች ስም የተሰማንን ደስታ እየገለፅኩ መጪው አዲስ ዓመት የኢትዮጵያ

በኢነርጂው ዘርፍ ባለፉት ሰባት ዓመታት እመርታዊ ለውጥ መመዝገቡ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ለሰባት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ በነበረው በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ በተዘጋጀው ሳይድ ኤቨንት ላይ ባደረጉት ንግግር ሀገራችን ከሀይል አቅርቦትም ሆነ ተደራሽነትን ከማሳደግ አንጻር አመርቂና አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቧን በመግለጽ ለዚህም ፖሊሲ በማርቀቅም ሆነ በማክ

ኢትዮጵየውያን በራሳችን የገንዘብ አቅም አይቻልም የተባለውን የህዳሴ ግድብ ገንብተን ያጠናቀቅንበት ዳግም አድዋችን ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ እለቱ ለኢትዮጵያውያን የአይቻልምን መንፈስ ሰብረን በራሳችን አቅም ዳግም አድዋ የሆነውን ታላቁ የህዳሴ ግድብን ያጠናቀቅንበት ድላችን በመሆኑ ኢትዮጵያውያንንና የኢትዮጵያ ወዳጆችን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

የሀሬ ወንዝ የመሬት አጠቃቀምን ፣ በውሃ አካላት የሚስተዋሉ ችግሮችን እና የብዝሀ ህይወት ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለውይይት ቀረቡ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተሠጠው ሀላፊነት አንዱና ትኩረት የተደረገበት የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፉ መሆኑን ጠቅሰው በዘርፉም ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት በዘላቂነት ለመጠቀም የውሃ አካላትን በተቀናጀ መልኩ የመጠበቅ እና የማስተዳደር ሀላፊነት

በየጭላ አበርገለ ወረዳ ከ483 ሚሊየን ብር በላይ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጀመረ

ፕሮጀክቱ በሀገር ደረጃ በድርቅ በሚጠቁ ወረዳዎች እየተተገበሩ የሚገኙ የአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም ፕሮጀክቶች አካል ሲሆን፤ ግንባታው በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ትብብር የሚከናወን ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በ HoARECN የሚተገበረው ፕሮጀክት ውጤታማ መሆኑ ተገለፀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በ Horn of Africa Regional Environment Center and Network (HoARECN) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዝዋይ ሻላ ሀይቅ ንዑስ ተፋሰስ ላይ የሚተገበረው ፓይለት ፕሮጀክት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራው የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም ፣ የውሃ ሀብት ግኝ

በኢነርጂ ሽግግር ፋይናንሲንግ እና በአየር ንብረት ኢንቨስትመንት ፕላትፎርም የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሠጠ ፡፡

ፕሮግራሙ በሀገራችን ቀጣይነት ያለው የሃይል አቅርቦትን ለማሳካት ትልቅ እመርታ እንዳለውና የኃይል ሽግግር አፋጣኝ ፋይናንሲንግ (ETAF) እና የአየር ንብረት ኢንቨስትመንት ፕላትፎርም (CIP) የአቅም ግንባታ ስልጠና ለዘርፉ ሙያተኞች መሰጠቱ ወሳኝ መሆኑን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የገጠር ኢነርጂ ልማት ቴክኖሎጂ ሽግ

Aug 2025

የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ንፅህና አገልግሎት ስርዓትን ማጠናከር (SCRS WaSH) የቴክኒክ ድጋፍ ፕሮጀክት በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ንፅህና አገልግሎት ስርዓትን ማጠናከር (SCRS WaSH) የቴክኒክ ድጋፍ ፕሮጀክት ስኬታማ መሆኑ በዩናይትድ ኪንግደም መንግስት፣ በኢትዮጵያ መንግስት፣ በዩኒሴፍ እና በቁርጠኛ የክልል ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነት ያሳያል ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ35ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለጸ።

ውሃና ኢርጂ ሚኒስቴር ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በጋራ ሲተገበር በቆየው የአረንጓዴ አየር ንብረት ፈንድ ፕሮጀክት (GCF project ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ35ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ አድርጓል ተብሏል።

በሁለተኛው ዙር የመንግስት አገልግሎት አስተዳደር ሪፎርም ላይ ውይይት ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የመጀመሪያው ዙር የመንግስት የአገልግሎት ሪፎርም ከአራት አመት በፊት ተግባራዊ መደረጉን አውስተው በአተገባበሩ የቀሩ ነገሮችን መለየትና እና ምን እየሰራን ነው የሚለውን መፈተሽ ይገባል ብለዋል።

ከ132 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ሆነዋል ተባለ።

በአረንጓዴ አየር ንብረት ፈንድ (Green Climate Fund) ፕሮጀክት ከ132 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ተምሩ ገደፋ ገለጸዋል።

የሁለተኛው ምእራፍ የአንድ ቋት ብሄራዊ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ኃይጅን ፕሮግራም የ2017 ዓ.ም አፈፃፀም እና የ2018 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መድረክ ተካሄደ።

የሁለተኛው ምእራፍ የአንድ ቋት ብሄራዊ የመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ኃይጅን (OWNP-CWA II) ፕሮግራም የ2017 ዓ.ም አፈፃፀምና የ2018 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ መድረክ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፥ ስራ አስፈፃሚዎች፥ የክልል ቢሮ ሃላፊዎች፥ የልማት አጋር ድርጅቶች፥ የፌደራልና ክልል ፐሮግራም ፈፃሚ

በውሃው ዘርፍ ላይ የሚታየውን የኢንቨስትመንት ክፍተት ለመሙላት መንግስታት ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት፣ ተስማሚ ፖሊሲ ማዘጋጀት እና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባቸው ተገለፀ ።

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በድቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የአፍሪካ የውኃ ኢንቨስትመንት ሰሚት ( AU AIP Africa Water Investment Summit 2025) የማጠቃለያ ዋና መድረክ ላይ በፓናሊስትነት በነበራቸው ተሳትፎ የኢትዮጵያን ተሞክሮ አካ

በኃይል አቅርቦት ኢንቨስትመንት ላይ ለመሠማራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዓለም አቀፍ ሶላር አሊያንስ ጋር በፀሐይ ኃይል ቴክኖሎጂ የሶላር ሚኒግሪድና የሶላር ፓርክ ፕሮጀክት ለመገንባት ስምምነት መፈራረማቸው በሶላር ፓርክና የሶላር ሚኒ ግሪድ የኃይል ማመንጫ፣ በመስኖና መጠጥ ውሃ አቅርቦት የፋይናንስና የቴክኖሎጂ ትብብር ዕድሎችን የሚያመቻች መሆኑን ክቡር ሚኒስትር

ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ለግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት የጀርባ አጥንት መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታውን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ የውኃ ኢንቨስትመንት ሰሚት (AU AIP Africa Water Investment Summit 2025) ጉባኤ የሁለተኛ ቀን የሚንስትሮች ከፍተኛ የፓናል ውይይት ላይ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ተጠይቀው ማብራሪ

ለዕይታ የቀረቡ የፈጠራ ስራዎች ንጹህ ኢነርጂን ተደራሽ በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ድርሻቸው የላቀ ነው ተብሏል፡፡

የቅድመ አፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽን ላይ ለዕይታ የቀረቡ የፈጠራ ስራዎች ንጹህ ኢርጂን ተደራሽ በማድረግ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ድርሻቸው የላቀ ነው ተብሏል፡፡

የሶስተኛው ምእራፍ ብሄራዊ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ኃይጅን ፕሮግራም ስትራቴጂ እና ማስፈፀሚያ እቅድ (OWNP III – Strategy and Action Plan) ተገመገመ።

ላለፉት አመታት ሲፈፀም የቆየው ሁለተኛው ምእራፍ ብሄራዊ የመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ኃይጅን (OWNP-II) ፕሮግራም አፈፃፀም ግምገማ ውጤቶችን መሰረት በማድረግ የተዘጋጀው የሶስተኛው ምእራፍ ብሄራዊ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ኃይጅን ፕሮግራም ስትራቴጂ እና ማስፈፀሚያ እቅድ (OWNP III – Strategy and Act

ከአለም አቀፍ ሶላር አሊያንስ (ISA) እና አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር የሚሰራው ስራ የኢትዮጵያን የኢነርጂ ሽግግር እንደሚያፋጥን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ገለጹ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚነስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር/ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከአለም አቀፍ ሶላር አሊያንስ (ISA) እና አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር የሚሰራው ስራ የኢትዮጵያን የኢነርጂ ሽግግር እንደሚያፋጥን፣ፈጠራን እንደሚያጎለብት እና ኢንቨስትመንቶችን እንደሚያበረታታ ገልጸዋል፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ 34ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ኬፕታውን ገብተዋል።

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የአፍሪካ ህብረት 34ኛው የመሪዎች ጉባኤ ውሳኔን ተከትሎ በህብረቱ አዘጋጀነት በደቡብ አፍሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የአፍሪካ የውኃ ኢንቨስትመንት ሰሚት ( AU AIP Africa Water Investment Summit 2025) ለመሳተፍ ደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የአለም አቀፍ የሶላር አሊያንስ (ISA) ዋና ዳይሬክተርን እና ልኡካኑን ተቀብለው አነጋገሩ።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአለም አቀፍ ሶላር አሊያንስ (ISA) ጋር ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ማሳደግ እና በዓለም አቀፍ የፀሐይ ሀይል በሚተገበሩ እና እየተተገበሩ ባሉ የ 400 ሜጋ ዋት የፀሐይ ፓርክን፣ የ700ኪሎዋት የሶላር ሚኒ ግሪድ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፣ Solar Wat

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋጭነትን ከመቀነስ አኳያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተች መሆኑን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ገለጹ፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የቅድመ ሁለተኛ የአፍሪካ አየር ንብረት ሰሚት የውሃና ኢነርጂ አውደ ርዕይን በይፋ በከፈቱበት መድረክ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ተጋጭነትን ከመቀነስ አኳያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ኢሉ ወረዳ በጣለዉ ከባድ ዝናብ የተነሳ ሁለት ቀበሌዎች ላይ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የተመራ ቡድን በኢሉ ወረዳ ተጅና አስጎሪ ቀበሌዎች የደረሠውን የጎርፍ አደጋ በስፍራው ተገኝተው ተመልክተው ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ4 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የንጽህና መጠበቂያ ሳሙናዎችን እና የውሃ ማከሚያ ኬሚካሎች በስፍራው ተገ

በዝዋይ ሻላ ንኡስ ተፋሰስ የሚተገበረው የሙከራ ፕሮጀክት ሰፋ ወዳለ ተፋሰስ ከፍ ተደርጎ ሊሰራበት በሚችል መልኩ ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚው አቶ ደበበ ደፈርሶ ፕሮጀክቱን ልዩ የሚያደርገው የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉና የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በምግብ ራስን ከመቻል ጋር በማስተሳሰር የሚተገበር መሆኑ ነው ብለዋል።

ከቻይና ኤግዚም ባንክ (Exim Bank) የ100 ሚሊየን ዶላር ብድር ለማግኘት የሚያስችል የትብብር የመግባቢያ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ብድሩ ሲገኝ በአምስት ከተሞች የመጠጥ ውሃና የሳኒቴሽ መሠረተ ልማት ግንባታን ለማከናወን መታቀዱን ገልፀዋል ።

የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስን ተደራራቢ ችግሮች ለመፍታት በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ገለጹ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በተዘጋጀው አውደ ጥናት መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስን ተደራራቢ ችግሮች ለመፍታት በርካታ ጥረቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል።

የዛሬ ስድስት ዓመት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ አገራችን ለአለም ምርጥ ተሞክሮ ያበረከተችበት ነው ሲሉ አቶ ማሙሻ ሀይሉ ገለጹ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የተመራ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በኦሮሚያ ክልል ገላን አራብሳ ወረዳ በንስላሌ ቀበሌ ተገኝተው በአንድ ጀምበር 700ሚሊየን ችግኞችን የመትከል ዘመቻን እውን አድርገዋል።

"እየተከልን ያለነው ችግኝ ብቻ ሳይሆን የምግብ ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን ያለንበት ሁነት ነው"!! ሀጂ አወል አርባ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንዲሁም የሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን ከሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላቶችና አመራሮችም በዕለቱ የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

የአሳይታ አፋምቦ የመጠጥ ዉሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ከ52 ሽህ በላይ የአካባቢው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገለጸ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በቀጣይ ሳምንት የመስመር ፍተሻ ስራዎች የሚጀመሩለት የአሳይታ አፋምቦ የመጠጥ ዉሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ከ52 ሽህ በላይ የአካባቢው ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡