Apr 2024

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሀይል ትስስር በመፍጠር የመሪነት ሚና እየተጫወተች መሆኑ ተጠቆመ፡፡

በአቡዳቢ እ.አ.አ ከአፕሪል 16 እስከ 18 /2024 እየተካሄደ በሚገኘው ወርልድ ፊውቸር ኢነርጂ ሰሚት (world Future Energy Summit) የጎንሽ መድረክ ላይ በመገኘት ገለጻ ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሀይል ትስስር በመፍ

174 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ኃይል ፕሮጀክት በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተገለፀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የተመራ ቡድን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንሶ ዞን ኬና ወረዳ ጌራ ቀበሌ ከGIZ እና ከክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ጋር በመተባበር እያስገነባው የሚገኘውን የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ጎበኙ።

የብሔራዊ ዋሽ ፕሮግራም ማኔጅመንት ዩኒት የዘጠኝ ወር አፈጻጸም ተገመገመ።

የዋን ዋሽ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ተስፋየ ሉሌ ፐሮግራሙ እንደ ሀገር በ50 ከተሞች በ308 ወረዳዎች እና በ42 የሲአር ዋሽ ወረዳዎች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተደራሽ የሚደረግበት በመሆኑ በክፍል ደረጃ በየጊዜው እየተገመገመ መመራቱ አፈጻጸማችን በማሻሻል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያግዛል ብለዋል

የኢነርጂ ሀብቶችን ፈጣን እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ በማልማት ተደራሽነትን ለማስፋት የሚያስችል ዘላቂ የሀይል ልማት ስትራቴጂ ይፋ ተደረገ፡፡

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በሰጡት ቃለ ምልልስ የኢነርጂ ፖሊሲው የግል ባለሀብቱን ተሳታፊነት የሚያጠናከር መሆኑን ጠቅሰው የፖሊሲውን አፈጻጸም ለማሳለጥና የግሉን ዘርፍ በልማቱ ተሳታፊ ለማድረግ አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂ ነው ብለዋል፡፡

የብሄራዊ የመጠጥ ውሃ፣ የሳኒቴሽን እና የኃይጅን የፕሮግራም ዝግጅት የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በለፉት አመታት መንግስት ለዜጎች ፍትሃዊ እና ዘላቂ በሆነ መልኩ ንፁህ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በፖሊሲና በስትራተጂ የተደገፈ ተጨባጭ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልፀዋል።

አንድን ተፋሰስ የእቅድ ማእከል በማድረግና ተዋናይ የሆኑ አካላትን በማሳተፍ የተቀናጀ ውሀ ሀብት አስተዳደርን ወደ መሬት ማውረድ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

የውሀ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ አንድን ተፋሰስ የእቅድ ማእከል በማድረግና ተዋናይ የሆኑ አካላትን በማሳተፍ የተቀናጀ ውሀ ሀብት አስተዳደርን ወደ መሬት ማውረድ እንደሚገባ ገልጸው

የአባይ ተፋሰስ ቤዚን ፕላን አተገባበር የመግባቢያ ስምምነት የፊርማ ስነስርዓት ተካሄደ፡፡

የአማራ፣ የኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ የውሀና ኢነርጂ ቢሮዎች፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ቢሮዎች፣ የአካባቢ ጥበቃ ቢሮዎች ኃላፊዎችና ተወካዮች በተገኙበት የአባይ ተፋሰስ ቤዚን ፕላን አተገባበር የመግባቢያ ስምምነት የፊርማ ስነስርዓት ከክልል የፕላንና ልማት ቢሮዎች ጋር ተደርጓል።

የአባይ ተፋሰስ ቤዚን ፕላን አተገባበር ፕላትፎርም ምስረታን አስመልክቶ ውይይት እየተደረገ ነው።

በሚኒስትር ድኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ እንደገለፁት የአባይ ቤዚን ከፍተኛ የህዝብ ብዛት እና የገፀ ምድር ውሃ ሀብት ያለው በመሆኑ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው አንጻር ትልቅ ትኩረት የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል።

የPRIM ፕሮጀክትን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል የ522.63ሚሊየን ዶላር የብድር ድጋፍ ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ መንግስት በሀይል ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ስራ እየሠራ መሆኑንና በፈረንጆቹ 2030 ሁሉንም የኢትዮጵያ ክፍል የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ እየተሰራ መሆኑን ፕሮጀክቱ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከአለም ባንክ የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጠና የመሰረተልማት ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ከአለም ባንክ የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ቀጠና የመሰረተልማት ዳይሬክተር Dr. Wendy Hughes ጋር በኢነርጂ ሴክተር ሪፎርም ዙሪያና ሌሎች የኢነርጂ ልማት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የኢፍጣር ፕሮግራም አካሄደ፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የበላይ አመራሮች በተገኙበት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች ጋር የአፍጥር ስነስርዓት ተካሂዷል።

የህዳሴ ግድብ እምቅ ሀብትን ለብልጽግና የማዋል ትልቁ ማሳያ ነው፡፡ ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ የኢፌድሪ ም/ጠ ሚኒስትር

የኢፌድሪ ም/ጠ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እምቅ ሀብትን አውጥቶ ለብልጽግና ማዋል የመንግስት ቁልፍ አጀንዳ መሆኑንና የዚህ ማሳያ ደግሞ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበት 13ኛ ዓመት ክብረ በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከበረ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሠረት ድንጋይ የተጣለበት ክብረ በዓል" በህብረት ችለናል" በሚል መርህ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በደመቀ ሁኔታ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ።

የውሃ አካላት ደህንነትን መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን ተገለፀ።

የእምቦጭ አረም የውሃ አካላት ላይ በመጠንም በጥራትም ጉዳት ከጊዜ ወደጊዜ እየተስፋፋ ስለሆነ ስትራቴጂክ እቅድ ተዘጋጅቶ በሰው ኃይልና በማሽን ለማስወገድ የተጀመረው ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል፤ ግድቦች ውሃ የመያዝ አቅማቸው እንዳይቀንስ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ጠቁመው፤ አረሙ በፍጥነት በመስፋፋት የሚያደርሰው ጉ

የእንቦጭ አረም ከቆቃ ሀይቅ የማስወገድ ዘመቻ የማስጀመሪያ መርሃግብር እየተካሄደ ነው፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የክቡር ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ኃይሉ እንደተቋም "ውሃ ህይወት ነው" የሚል መርህን አንግቦ የሚሰራ በመሆኑ ውሃን ስንጠቀም እንዳይበከልና እንዳይባክን በአግባቡ ልንጠብቀውና ልንንከባከበው እንደሚገባ ገልፀዋል።

Mar 2024

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ስቴፋን አወር ጋር ተወያዩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የጀርመን አምባሳደር ስቴፍን አወር እና የሳይመንስ (SIEMENS ENERGY) ኩባንያ ተወካይ ጋር በኢነርጂ ልማት ኢንቨስትመንት ዙሪያ ተወያዩ፡፡

ግድቤን በደጄ ፕሮጀክት ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የክቡር ሚኒስትሩ የኮሙኒኬሽን አማካሪ ወ/ሮ ገበያነሽ ነጋሽ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ንጹህ የመጠጥ ውሃን ተደራሽ ለማድረግ በመጠጥ ውሃና በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፎች በርካታ ስራዎቾ እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰው ውሃ አላቂ ሀብት በመሆኑ በእንክብካቤ፣ በቁጠባና በንጽህና ይዘን እያለማን መጠቀም አለብን ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበሩ፡፡

የክቡር ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ኃይሉ ሴቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፍ ያላቸውን ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አበረታች ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል፡፡ የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግና ተጠቃሚነታቸውንም ለማረጋገጥ ሥራዎች ታቅደው እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡

የአለም ውሃ ቀን "ውሃን ለሰላም" በሚል መሪ ቃል ተከበረ።

የክቡር ሚኒስትር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ ውሃ ሂወት ነው ስንል ሂወት ላለው ነገር በሙሉ መሰረት መሆኑን እንደሚያሳይና ውሀን ለሰላም ስንል ደግሞ ዘርፈ ብዙ ለሆኑ ጉዳዮች እንደሚያገለግልና ጥቅም ላይ በምናውልበት ጊዜ በፍትሀዊነትና በስምምነት ለሁሉም በሚበቃ መልኩ መጠቀም የምችልበትን ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር ነ

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን መሬት ላይ ለማውረድ የተፋሰስ እቅድ አንዱ መሳሪያ ነው ተባለ።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በተፋሰስ ውስጥ ያሉትን ሀብቶች ለልማት ለማዋል ያስችል ዘንድ ሁሉም አካላት በጋራ የሚያቅዱበትና በጋራ ሪፖርታቸውን የሚገመግሙበት እንዲሁም አንድ እቅድ አንድ ሪፖርት በሚል መርህ የተፋሰሱን ሀብት በጋራ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚቻልበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተዘጋጀ ያለ እቅድ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአፍሪካ ልህቀት ማዕከል ጋራ በጋራ መስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

ከፊርማ ስምምነቱ በኋላ ለጋዜጣኞች ማብራሪያ የሰጡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን፣ በውሃ ሀብት አስተዳደር እና በኢነርጂ ልማት ዘርፎች በጋራ መስራት የሚያስችል የአቅም ግንባታ በተቀናጀ መልኩ ከማዕከሉ ጋር ስምምነት መደረጉን ገልጸዋል።

ከፈረንጆቹ 2013 ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የናሽናል ዋን ዋሽ ፕሮግራም ሁለተኛውን ምእራፍ በማጠናቀቅ ሶስተኛውን ምእራፍ ለመጀመር የሚያስችል የውይይት መድረክ ተካሂዷል፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋ ዲንጋሞ መንግስት ለዜጎች ንጹህ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎትን በፍሃዊነትና በዘላቂነት ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ እና ይህንን እውን ለማድረግም ፖሊሲና ስትራቴጅ ተቀርጾ በመተግበር ላይ መሆኑን ግልጸዋል፡፡

የምስራቅ ኢትዮጵያን የሀይል መቆራረጥ ችግር ለመፍታት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ::

በምስራቁ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ የሆነ የሀይል እጥረትና መቆራረጥ ችግርን ለመፍታት ታላሚ ያደረገ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ ክቡር ደ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ገልጸዋል ፡፡

ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት አበረታች መሆኑ ተጠቆመ።

ተቋሙ ለመጠጥ ውሃው ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ፤ ከከተሞች መስፋፋት ጋር ተያይዞ ለውሃ አቅርቦት የሚያገለግሉ ግብዓቶች የዋጋ ንረትን ታሳቢ ያደረገ ጋይድላይን በመሆኑ በዶክመንቱ ላይ ከባለድርሻዎች ጋር ለመወያየት የተደረገውን ጥረት አድንቀዋል።

በዋርዴር ወረዳ ኩርቱሌ ቀበሌ የሶላር ኢነርጂ ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ተቋሙ የኢነርጂ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ ከግሪድ ውጭ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ አማራጭ ኢነርጂ ላይ እየተሰራ መሆኑንና እየተገነቡ የሚገኙ የሶላር ቴክኖሎጂ፣ የባዮ ጋዝ እንዲሁም የንፋስ ሀይል ማሳያ መሆናቸውን ተናግ

የከተማ ውሃ አቅርቦት ጥናትና ዲዛይን መመዘኛና መለኪያ ጋይድላይን ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ጥናትና ዲዛይን ጋይድላይን ችግር ፈቺ እንደሚሆን ገልፀው፤ በመድረኩ የሚሰጠው አስተያየት ዶክመንቱን በማጠናከር የበለጠ እንዲዳብርና የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ይሆናል ብለዋል።

በስምጥ ሸለቆ ሐይቆች በሰገን ወንዝ ላይ ለሚገነባ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የቅድመ ጥናት ረቂቅ ሪፖርት ለውይይት ቀረበ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ሀብት ጥናት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሌብ ታደሰ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በፌዴራል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የውሃና ኢነርጂ ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ዘርፍ የፕሮጀክቱ ዲዛይን ጥናት በመካሄድ ላይ መሆኑን ገልፀው፤

ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገዙ 13 ኮምፒዩተሮችን ለከተሞች ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ፅ/ቤቶች ድጋፍ ተደረገ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ድጋፉ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የውሃ አገልግሎት ተቋማትን አቅም ለማጎልበት ከሚያደርገው ድጋፍ አንዱ መሆኑን ገልፀው፤ የውሃ አገልግሎት ስራውን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግና ፈጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰዋል።

128ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተከበረ፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ባስተላለፉት መልእክት፤ የኢትዮጵያ ህዝቦች በአንድ ጥሪ ተሰባስበው የኢትዮጵያን ወራሪ ኃይል ድል ማድረጋቸው የህዝባችንን አንድነትና በጋራ ጥቅሞቻችን ላይ መተባበርን እንደሚያመለክት ገልፀዋል።

''ሴቶችና አመራርነት'' በሚል ርዕስ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሴቶች ስልጠና እየተሠጠ ነው።

የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኦልቀባ ባሼ ሴቶችን ወደ አመራር ሰጭነት ለማምጣት እና ተወዳዳሪነትን ለማሳደግ እንዲሁም በአመራር ላይ ያሉ ሴቶችን ደግሞ ብቃታቸውን ለማሳደግ ታላሚ ያደረገ ነው ሲሉ የስልጠናውን አስፈላጊነት ገልጸዋል።

የአዳማ ከተማ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አፈፃፀም 64% መድረሱ ተገለፀ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በሕ/ተ/ም ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የመሰረተልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትና የጨፌ ኦሮሚያ የመሰረተልማት ቋሚ ኮሚቴ አስተባባሪዎች ጋር በነበራቸው የሁለት ቀን የመስክ ምልከታ ቆይታ አስመልክቶ በዋና ዋና ጉዳዮች

Feb 2024

በሞጆ ከተማ አስተደደር በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ድጋፍ ለአቅመ ደካሞች የተገነባ መኖሪያ ቤት ለተጠቃሚዎች ቁልፍ ርክክብ ተደርጓል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ባለፈው ክረምት በሞጆ ከተማ አካባቢ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ላይ የቤት እድሳት መርሃግብር መጀመሩን ገልጸው የመኖሪያ ቤት ለተሰራላቸው ለ25 አቅመ ደካሞች ሙሉ አልባሳት ድጋፍ ተደርጓል ።

በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ቡድን በግምቢቹ ወረዳ የተለያዩ የመጠጥ ውሃና ኢነርጂ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ዘንድሮ በተለያዩ ክልሎች ተመሳሳይ የመስክ ምልከታ መካሄዱን አስታውሰው፤ የጉብኝቱ ዋና አላማም በአፈፃፀም ሂደት ያጋጠሙትን ችግሮች በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ እና ክልሎችንም ለመደገፍ ታሳቢ ያደረገው መሆኑን ገለፀዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ከዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከዋልታ ሚዲያ ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት አመራሮች ጋር የውሃና ኢነርጂ ጉዳዮችን ሚዲያን ተጥቅሞ ዜጎችን ከማስተማርና ዘርፉን ከማስተዋወቅ አንጻር ውይይት አድርገዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ፎረም መመስረቻ ደንብ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡

የክቡር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የዛሬው አጀንዳ ስራችንን ለማስፋት ከክልሎች ጋር በቅንጅት የበለጠ ለማጠናከር፤ የምንሰራቸው ስራዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፤ መመሪያውን በዚህ ደረጃ ለማስፈጸም ታስቦ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነው ብለዋል፡፡

የብሔራዊ የንፁህ ማብሰያ ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ዙሪያ ምክክር ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ሀገራችን በኢትዮጵያ የተሻሻለ የባዮማስ ምግብ ማብሰያዎችን በማስተዋወቅ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ የንፁህና ኢነርጂ ቆጣቢ ማብሰያ ተደራሽነትን ሽፋን ከ10 በመቶ በታች በመሆኑ ከ90% በላይ ህዝባችን ለምግብ ማብሰያነት ጥቅም ላይ የሚውለው ማገዶ ደን በመመንጠር ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የናይል ተፋሰስ ትብብርን እውን ለማድረግ ግንባርቀደምነቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተገለጸ፡፡

በቡሩንዲ ቡጁምቡራ እየተካሄደ በሚገኘው 25ተኛው የናይል ቀን እየተሳተፉ የሚገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ኢትዮጵያ የናይል ተፋሰስ ትብብርን እውን ለማድረግ ግንባር ቀደምነቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጹ፡፡

''የውሃ ሀብታችን ለብልፅግናችን'' በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው ሀገራዊ ኤግዚብሽን ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና መርሀ ግብር ተካሔደ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ኤግዚብሽኑ ዘላቂ የውሃ ሀብታችንን እንዴት እንደምናስተዳድር፣ የኢነርጂ ልማትን በማስፋፋት፣ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘረፍ የሚከናወኑ ስራዎቻችንን ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የፈጠረልን ነው ብለዋል።

500 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በውሃ የሚሠራ የአነስተኛ ኃይል ማመንጫ በአለታ ወንዶ ወረዳ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የተመራ ቡድን 500 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በውሃ የሚሠራ መካከለኛ የኃይል ማመንጫ ጎብኝተዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የጎርፍ አደጋን የመከላከል ስራን በተጠናከረ መንገድ ለመፈጸም ሚያስችል ስልጠና ለባለድርሻ አካላት ተሰጠ።

ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የጎርፍ አደጋ ለመከላከል በተቀረጸ ፕሮጀክት ላይ መሰረት አድርጎ የጎርፍ መከላከል ስራን በተጠናከረ መንገድ ለመፈጸም ሚያስችል ስልጠና ተሰጠ።

በሲዳማ ክልል በሐዋሳ ከተማ ዙሪያ በኤሌክትሪክ ኃይል መስኖን የሚያለማ ፕሮጀክት ለአገልግሎት ዝግጁ መሆኑ ተገለፀ።

በሲዳማ ክልል ጉብኝት ላይ ያሉት የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የተመራ ቡድን ከሰዓት በኋላ በሲዳማ ክልል በሐዋሳ ከተማ ዙሪያ በኤሌክትሪክ ኃይል መስኖን የሚያለማ ፕሮጀክት በጎበኙበት ወቅት በሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ ኃይል በመጠቀም መስኖን ለማልማት እየተደረገ ያለው ጥረት አድን

ክቡር ሚኒስትሩ ከአፍሪካ የልማት ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር ተወያዩ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የአፍሪካ ልማት ባንክ የሀይል፣ የአየር ጸባይና አረንጓዴ ልማት ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት ሚ/ር ኬቨን ካሩኪ ጋር በታዳሽ ሀይል ልማት እና ተያያዥ የልማት አጀንዳዎች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡