May 2026

ግዙፉ የገልጨት-ሰሪቴ የውኃ አቅርቦት ፕሮጀክት የህብረተሰቡን ህይወት የሚቀይር ነው። ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሮጀክቱ ድርቅን ከመከላከል ባለፈ የሕዝብ ጤናን በማስጠበቅ፣ የነዋሪዎችን መተዳደሪያ አቅም በማጠናከር እና መጪው ትውልድ የሚጠቀምበትን የግብርና እምቅ አቅም በማዘጋጀት ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክተዋል።

በሰብዓዊነት የታጀበ ልማት፡ የአቅመ ደካማ ዜጎች ቤት እድሳትና ግንባታ ውጤታማ ስራዎች፡

በመላው ሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች የነበሩ የፈራረሱ፣ ለዝናብና ለነፋስ ተጋላጭ የሆኑ እና ለኑሮ አስጊ የነበሩ ቤቶች ተጠግነው እንዲሁም አዲስ ተገንብተው ለባለቤቶቻቸው ተረክበዋል። ከዚህ በፊት የሰው ልጅ ሊኖርበት በማይችል ሁኔታ ዝናብን እየተቀበሉ ይኖሩ የነበሩ ቤተሰቦች ዛሬ የተሻለ የመኖሪያ ሁኔታ አግኝተዋል።

ከ34 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ለ115 ከተሞች ተሰጠ።

ሚኒስቴሩ በዘርፉ የሚተገብራቸው የድጋፍ ማዕቀፎች በሁለት ዋና አቅጣጫዎች የተደራጁ ሲሆን፣ አንደኛው “ቀጥታ ድጋፍ” ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በኢትዮጵያ የውሃ ፖሊሲ መሠረት “ወጪን በማስመለስ” መርህ ላይ የተመሠረተ የብድር ሥርዓት መሆኑን የውሃ ልማት ፈንድ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዶጊሶ ጎና ገልጸዋል።

ከ88 ሺ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የሾኔ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ልማት ፈንድ መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዶጊሶ ጎና እንደገለፁት፣ ፕሮጀክቱ የባስኬት ፈንድ ፕሮጀክት አካል ሲሆን የፋይናንስ ድጋፉ ከአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ፣ ከጣሊያን ልማት ድርጅት እና ከፈረንሳይ ልማት ድርጅት የተገኘ ሲሆን፣ ከ383 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ብለዋል።

የኢነርጂ ረቂቅ ፖሊሲ ጸደቀ

ፖሊሲው ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ ከአሥር አመቱ የልማት ዕቅድ፣ ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማት ስትራቴጂ፣ ከምዕተ አመቱ የልማት ግቦች እና ከሌሎች ፖሊሲዎች ጋር የተጣጣመ መሆኑ ተገልጿል።

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር በሚሰሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጨባጭ ውጤት እየመጣ ነው ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል የሆነው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን የተገነባው የ1ኛ ጤፎ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የምረቃ ስነስርዓት ላይ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር በሚሰሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተጨባጭ ውጤት እየመጣ መሆኑ ተገለፀ።

የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም (One WASH National Programme - OWNP) ባለፉት ስድስት ዓመታት አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ።

የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ አብይ ግርማ አራት ቁልፍ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን ውሃና ኢነርጂ፣ ጤና፣ ትምህርት እና ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲሁም የልማት አጋሮችን በማስተባበር በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

የግድቤን በደጄ የሦስት ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአስቸኳይ ጊዜና ልዩ ድጋፍ ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ሠላማዊት ተወልደ እንደገለፁት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ንጹህ የመጠጥ ውሃን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ከገጸ- ምድርና ከከርሰ -ምድር የውሃ ሃብት በማቅረብ ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት በማጠናቀቅ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታምሩ ገደፋ ተቋሙ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽንን ዘርፍ ለማሻሻል የ10 ዓመታት መሪ ዕቅድ በመንደፍ በተለያዩ ክልሎች የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ ሆኗል ብለዋል።

የሂውማን ካፒታል ኦፕሬሽን (HCO) ፕሮጀክት የባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

በሚኒስትር ድኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪና የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የሚኒስትር ድኤታ ተወካይ አቶ ሞቱማ መቃሳ የሂውማን ካፒታል ኦፕሬሽን (HCO)ፕሮጀክት በውሃና ኢነርጂ፣ በትምህርት፣ በግብርና፣ በጤናና በሴቶችና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያቤቶች ቅንጅት፣ ትብብርና በጋራ ዕቅድ የሚተገበርና የሚመራ

የተቀናጀ አስተዳደር የውሃ ሀብትን ለቀጣይ ትውልድ ጠብቆ ለማስተላለፍ

የውሃና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶችን በተቀናጀ መልክ ለማልማት ሀገሪቱ ያሏትን ተፋሰሶች መሰረት ባደረገ መልኩ ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚያስፈልገው የውሃ አለኝታ እንዲኖር ለማድረግ የውሃ አካላትን ደህንነት ለመጠበቅ በማቀድ እየተሰራ ነው።

የተቀናጀና ዘላቂ የመሠረተ ልማት እና ሀብት ቁጠባ በመደመር እሳቤ!

በለውጡ መንግስት በመደመር እሳቤ የአንድን ሀገር የኢኮኖሚ ጥንካሬና የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ኃይልና የንፁህ መጠጥ ውኃ ተደራሽነት ማረጋገጥ እጅግ ወሳኝነት አለው።

ፕሮጀክቱ የውሃ ሀብታችን ለብልፅግናችን የሚለውን መርህ የሚያረጋግጥ ነው። /ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለዜጎች ንፁህ የመጠጥ ውሃና የሳኒቴሽን አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የሰራው ፕሮጀክት የውሃ ሀብታችን ለብልፅግናች የሚለውን መርህ የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።

የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የሶስተኛው ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ደገፉ ፣ ፕሮጀክቶች በመጀመሪያና በመጨረሻ ደረጃ ላይ ፈተና እንደሚያጋጥማቸው ጠቅሰው፣ የተጀመሩ ስራዎችን በቀሪው አጭር ጊዜ በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የዜጎችን ኑሮ እያሻሻለ የሚገኘው የኃይል አቅርቦት

ህብረተሰቡን በኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ (ግሪድ) ጋር የተገናኙ እና ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ ውጪ በሆነ የኃይል አማራጭ (ኦፍ ግሪድ) የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ በሚደረገው ጥረት ውጤት እየተመዘገበ ነው።

የከተማ የውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረገ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፥ በኢትዮጵያ፣ ፈጣን የከተማ እድገት በነባሩ የሳኒቴሽን መሠረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል፤ የከተሞች በፍጥነት መስፋፋት ለሚሊዮኖች የተገቢ የፍሳሽ ቆሻሻ አያያዝ አገልግሎት አለመኖር ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነ ጠቅሰው፤ ችግሩን ለመፍታት በትኩረት እየተ

ሁለተኛ የከተሞች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት እስካሁን በተሰሩ ስራዎች በመጡ ውጤቶችና በቀጣይ ምዕራፍ ስራ የግምገማ ወርክሾፕ ተካሄደ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሳኒቴሽን መሠረተ ልማት ዋና ስራ አሰሰፈጻሚ አቶ ኑረዲን መሀመድ ወርክሾፑ በዘርፉ እስካሁን የተሰሩ ስራዎችን ለመገምገምና ቀሪ ስራዎችን በተያዘላቸው ጊዜና በጀት ለማጠናቀቅ ወሳኝ መድረክ ነው ብለዋል።

ከ450 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የዳዬ ከተማ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ፕሮጀክቱ የዳዬ ከተማ ሕዝብ የረጅም ጊዜ የንፁህ መጠጥ ውሃ ጥያቄ የመለሰ መሆኑን ገልጸው ንፁህ ውሃ ማቅረብ ጤናማና አምራች ዜጋ ለመፍጠር ወሳኝ በመሆኑ ህብረተሰቡ ተቋሙን በጋራ የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት

ኢትዮጵያ በታዳሽ ሀይል (Renewable Energy) ልማት ረገድ በአፍሪካ አልፎ ተርፎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ እምቅ አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ሆና ተጠቃሽ ስፍራ ይዛለች።

የኢትዮጵያ የወደፊት እድገት ከታዳሽ ሀይል ልማት ጋር በቅርብ የተሳሰረ በመሆኑ ሀገሪቱ የሀገር ውስጥ የሀይል ፍላጎትን ለማሟላት፣ የኢንዱስትሪ እድገትን ለማፋጠንና የአፍሪካ የሀይል ማዕከል ለመሆን እያደረገች ያለው ጥረት ተስፋ ሰጪ ነው። ለዚህ ስኬት መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ቀዳሚውን ስፍራ ይወስዳል።

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ወደ ተግባር የገባው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ግብርና፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም፣ ኢንዱስትሪ እና አይቲ ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበ ይገኛል።

አሁን ባለው ተፈላጊነት የሚመረተው ታዳሽ ኃይል በዚህ ዓመት 23 በመቶ ላደገው የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት ምላሽ ሰጥቷል። ክቡር የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) በታዳሽ ኃይል ዘርፍ ኢትዮጵያ ከምን ጊዜውም በተሻለ ሁኔታ በርካታ ስራዎች እየሰራች መሆኑን ያነሳሉ።

በኦሞ-ጊቤ ተፋሰስ ዕቅድ ቴክኒካል ቡድን የኦዲት ሪፖርት ክለሳ ዙሪያ የተዘጋጀው የባለድርሻ አካላት መርሃ ግብር በርካታ ግብዓቶች ያገኘንበት በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።

የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር ዕቅድ ትግበራን ለማሳካት በስራ ሃላፊነታችን የተሰጠንን ተልዕኮ ለማሳካት በርካታ ግብዓቶች ያገኘንበት በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

የተፋሰስ ዕቅድ ትግበራን በማረጋገጥ የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደርን ዕውን ማድረግ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል-አቶ ደበበ ደፍርሶ

ኢትዮጵያ 12 ተፋሰሶች ያሏት ሃገር እንደመሆኗ መጠን እነዚህ ተፋሰሶች የውሃ ሃብታቸው የውሃ ፍሰት ወሰንን የተከተለ በመሆኑ ይህንን መሠረት በማድረግ በክልሎችና በሴክተሮች ማዕከል ያሉትን የተለያዩ ስትራቴጂክ ዕቅዶች በማሰባሰብ የዕቅድ አሃድ አድርጎ በመውሰድ ዋናው የተፋሰስ ዕቅድ የሚዘጋጅ ነው።

የኦሞ -ጊቤ የተፋሰስ ዕቅድ ቴክኒካል ኦዲት ሪፓርት የባለድርሻ አካላት መድረክ እየተካሄደ ነው።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የኦሞ-ጊቤ ወንዝ 79,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ያለውና 7.2 በመቶ ሽፋን የሚሰጠው ስለሆነ የሃገሪቱ ትልቅ ሃብት ነው በማለት ያብራሩ ሲሆን ወንዙ ወደ ቱርካና ሃይቅ የሚፈስ በመሆኑ ኢትዮጵያም ለዚሁ ሃይቅ ሰፊ ድርሻ እንዳላት አብራርተዋ

የአንድ_ቋት ዋሽ (oneWASH) ማኔጅመንት ኢንፎርሜሽን ሲስተም (MIS) ማሻሻያ የመነሻ ሪፖርት /Inception Report /ወርክሾፕ ተካሄደ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ አስተማማኝና ውጤታማ የመረጃ ስርዓት ትክክለኛ ዕቅድ ለማቀድ፣ለውሳኔ አሰጣጥ ፣ክትትል ለማድረግና ተጠያቂነትን ለማስፈን እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አረንጓዴ ዐሻራ ለዘላቂ የውሃ ሃብት ልማት ጥበቃ ቀዳሚ መፍትሔ!

በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ የተጀመረው መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል ባሻገር ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሀብቶቻችን ዋስትና የሰጠ ውጤት አስመዝግቧል። በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ ውስጥ 18

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከጃፓን አለምአቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) ጋር ቀጣይ በትብብር በሚሰሯቸው ጉዳዮች ላይ መከሩ።

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ታምሩ ፈቃዱ በ JICA እና EWTI መካከል ያለው ትብብር እ.ኤ.አ 1998 ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ከJICA ጋር የረጅምና ትርጉም ያለው ታሪክ እንዳላቸው አስታውሰው፤ የቴክኒክና ተቋማዊ ድጋፎችን በማድረግ የሰው ኃይል አቅማችንን፣ ቴክኒካል ብቃታችንን፣

በኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኃይድሮጂን ልማትና አጠቃቀም ስትራቴጂን ወደ ተግባር ለመቀየር ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መድረክ ተካሄደ።

የኢነርጂ ሃብት ጥናት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሌብ ታደሰ በበኩላቸው በኢትዮጵያ ከምርት ተቋማት የሚወጣውን በካይ ጋዝ ለመቀነስ፣ ከውጭ የሚገባውን ነዳጅ በማስቀረት የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለማዳንና፣ ከሀገር ውጭ ግዢ የሚደረግበትን ኢአሞኒያ ማዳበሪያ በሃገር ውስጥ አምርቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስትራቴጂ ለመቀየስ መድረኩ

የዘፊኔ ከተማን የንፁህ መጠጥ ውሃ ና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የህብረተሰቡን ችግር በዘላቂነት እንደሚፈታ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋም ፕሮጀክቱ የዘፍኔ ከተማ በቺላሼ ቀበሌ የሚኖሩ ከ34,118 በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልጸው ለከተማው ነዋሪዎች አስተማማኝና ዘላቂ የውሃ አቅርቦት ከመስጠቱም በላይ በተለይ ውሃ ፍለጋ ረጅም ርቀት የሚጓዙ ሴቶችንና ህፃናትን የጊዜና የጉልበት ብክነት የሚያስቀር ከመሆኑም

በቤና-ጸማይ ወረዳ የቀይ አፈር ከተማ ከ15 ሺ በላይ ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸው ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በክልሉ እንደ ፌደራል መስሪያ ቤት በኢነርጂ፣ በውሀ ሀብት አስተዳደር እንዲሁም በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ትላልቅ ፕሮጀክቶች እየተሠሩ መሆኑን ገልጸው የቀይ አፈር መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው ብለዋል።

በትምህርትና ጤና ተቋማት ዘላቂ የኤሌክትሪፊኬሽን አቅርቦትና የክፍያ ሥርዓት ላይ ውይይት ተካሄደ።

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሲሆኑ፣ ላለፉት አራት ዓመታት ለኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሞች ልዩ ትኩረት በመስጠት በኃይል ዘርፍ ላይ ሪፎርም ከመካሄዱ ጀምሮ በርካታ ውጤታማ ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል ።

ከ 135 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የሆቢቻ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ በሺዎች የሚቆጠሩ የሆቢቻ ወረዳና የአካባቢው ቀበሌ ነዋሪዎች ንፁህ ውሃ ማግኘት መጀመራቸውን ገልጸዋል።

የጨለለቅቱ ከተማ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክብር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የከተማዋን ለዘመናት የቆዬ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፍላጎት ጥያቄ መሠረት ከ182 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ከፌደራል መንግስት በጀት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሲአር ዋሽ በኩል ተሰርቶ ለዚህ በቅቷል ብለዋል።

ከግሪድ ውጪ የሆኑ ማህበረሰብን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግና የሶላር ቴክኖሎጂን በዘላቂነት ለማስቀጠል የአቅም ግንባታ ስልጠና ወሳኝ ነው ተባለ፡፡

የኤሌክትሪፊኬሽንና ኢነርጂ መረጃ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ከግሪድ ውጪ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከመቼውም በበለጠ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ የሶላር ቴክኖሎጂን በዘላቂነት ለማስቀጠል የአቅም ግንባታ ስልጠና ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

የየትኛውም የልማት ስራ ዕቅድ መነሻው ተፋሰስ/ውሃ ሀብት/ መሆኑ ተገለፀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚተገበር በብራይት/BRIGHT/ ፕሮጀክት የተዘጋጀ የአባይ ተፋሰስ ዕቅድ ቴክኒካል ኦድት ተደርጎና ተከልሶ በተዘጋጀ ዕቅድ በአተገባበር ምዕራፍና ዕቅዱን በማዳበር ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።

ኢትዮጵያና አዘርባጃን በውኃና ኢነርጂ ዘርፍ የትብብር እድሎችን ለማጠናከር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ተፈጥሮ የለገሳትን ሀብት በመጠቀም የህዝቦቿን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስና የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል ከህብረተሰቡ እና ከልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በርካታ ስራዎችን እያከናወነች መሆኗን ገልጸዋል።

የአባይ ተፋሰስ ዕቅድ ቴክኒካል ኦዲት እና የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር የሀብት ማፕንግ/resource mapping /ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚተገበር በብራይት /BRIGHT /ፕሮጀክት የተዘጋጀ የአባይ ተፋሰስ ዕቅድ ቴክኒካል ኦዲት እና የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር የሀብት ማፕንግ/resource mapping / የባለድርሻ አካላት ወርክሾፕ ሌክአቬኑ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

በሶላር ቴክኖሎጂ ከግሪድ ውጪ ለሆነው ማህበረሰብ ኤሌክትሪፊኬሽንን ለማረጋገጥ የክልልና የግሉ ዘርፍ ሚና የላቀ ነው።

የኤሌክትሪፊኬሽንና ኢነርጂ መረጃ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ፕሮጀክቱን ለመተግበር በተደረገው የዳሰሳ ጥናት መሰረት የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ጠቁመው፤ በተቀናጀ የዲዛይን አቀራረብ ለመተግበር የግሪድ መዳረሻ ቦታዎች ላይ ኤሌክትሪክን ተደራሽ ለማድረግ እና ከግሪድ ውጪ ለሆነው ማህበረሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ የኤ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የመሩት ቡድን የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖን ጎበኙ።

በጉብኝቱ ወቅት ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ እንደገለጹት በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ከ70 በመቶ በላይ የውሃ ግንባታ ማቴሪያሎች በውጭ ምንዛሬ ላይ የተመሠረቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ እነዚህን በአገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው አመልክተዋል።

ብራይት ፕሮጀክት ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ የሚወገደውን ቆሻሻ ውሃ በማከም ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል ስምምነት ፈጸመ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚተገበረው የብራይት (BRIGHT) ፕሮጀክት ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ የሚወጣውን ቆሻሻ ውሃ በማከም መልሶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል ስምምነት ፈጸመ።

በውሃና መሬት ሃብት ማዕከል በኮምፒውተር አሰራር የታገዘ አዲስ ሞዴል ለግምገማ ቀረበ።

ሞዴሉ የተዘጋጀበት ምክንያት አስቀድሞ በሃገሪቱ በተመረጡ የገጠር አካባቢዎች ከአርሶ አደሮች ጋር የጋራ ውይይት በማካሄድ አሁን የሚጠቀሙበትን የአስተራረስ ዘዴና ስልተ ምርት በመለየት ማሻሻል የሚችሉበትን መንገድ ለመቀየስ አዳዲስ ተሞክሮዎችን እንዲተገብሩ ለማስቻል መሆኑን አስረድተዋል።

ስልጠናው የትግራይ ክልልን የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ጥያቄ በሚመልስ መልኩ ለመተግበር ያግዛል ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ከግሪድ ርቀው የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የኢነርጂ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚተገብረው የአደሌ ፕሮጀክት የአቅም ግንባታ ስልጠና አንዱና ዋነኛው በመሆኑ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ማጠቃለያ መርሃግብር ላይ የትግራይ ክልልን በኢነርጂ

የኢነርጂ ዘርፍ የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና በመጣው ለውጥ ውይይት ተደረገ ።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ በኢነርጂው ዘርፍ የሚመሩና የሚተገበሩ በርካታ ፕሮጀክቶች እንዳሉ አውስተው በአጠቃላይ ባለፉት 9 ወራትም ይሁን በ5ቱ ዓመታት ጉዞ በዘርፉ የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ለኢባላ-አዲሎ ከተማ ከመጠጥ ውሃ ግንባታ፣ የኤሌክትሮሜካኒካል አቅርቦትና ተከላ ፕሮጀክት ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከምባታ ዞን ለምትገኘው ለኢባላ-አዲሎ ከተማ ከመጠጥ ውሃ ግንባታና የኤሌክትሮሜካኒካል አቅርቦትና ተከላ ፕሮጀክት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ።

Apr 2026