Jan 2026

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የአዳማ ከተማ የፍሳሽ ማጠሪያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራን በይፋ አስጀመሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ መቀሌ ላይ ያስጀመርነውን የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት አዳማ ላይ ለማስጀመር ከአለም ባንክ በተገኘ 1.9 ቢሊን ብር በሚሆን ወጭ ተገንብቶ በቀጣዮቹ 18 ወራት ይጠናቀቃል ብለዋል።

የዘርፉን ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ቴክኒካል ክፍተቶችን በመሙላት በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ውጤታማ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልጠና ነክ ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዜርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ የአቅም ግንባታ ስልጠናው ከዚህ ቀደምም ይሰጥ እንደነበረ ገልፀው ስልጠናው ቴክኒካል ክፍተቶችን ለመሙላት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዱለው ተናግረዋል።

ሶስት አማካሪዎች ከአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች በ55ቱ ወረዳዎች ከሚገነቡት መካከል እስከአሁን ድረስ የ22 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመገባደድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከ82,000 የማህበረሰብ

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ጥበቃ ስራን በተሻለ ንቅናቄ ለመምራት የሚያስችል የትግበራ ስምምነት ተፈረመ።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ የባዘርኔት ፕሮጀክት በመጀመሪያው ምእራፍ እየተገበረ ያለው የአቅም ግንባታና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በመሆኑ በክልሉ ያሉ አካላትን በፕሮጀክቱ አተገባበር ላይ ያላቸውን አቅም ማጠናከርና ማዘጋጀት በእጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል /WLRC/ ጋር በጋራ በመቐለ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ ላይ የሚተገበረው የብራት ፕሮጀክት በተሰራው የዳሰሳ ጥናት ዙሪያ በሚካሄደው የውይይት መድረክ ላይ ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለ

የ2018ዓ.ም. የግድቤን በደጄ ፕሮጀክት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አስፈጻሚ አካላት የስልጠና መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

የንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ አነሳሽነት የተጀመረ ሲሆን ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በተለያየ መንገድ የሚገኘውን ውሃ በማሰባሰብ እጥረት በተከሰተ ወቅት ጥቅም ላይ የሚያውሉ

የሶላር ሚኒግሪድ ስራዎችን በህብረት ስራ ኤጀንሲዎች ለማስተዳደር የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው።

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ስልጠናው በዋናነት የአፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም UNDP ፕሮጀክት የሚተገብራቸው ሚኒ ግሪዶች በህብረት ስራ ሞዴል መሆኑን ገልጸው እነዚህ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ ህብረት ስራዎችን በማደራጀት በሚኒግሪድ ዙሪያ ያላቸውን መረዳት ለመጨመር ስራውን ለማስተዳደ

በፍትሃዊነት ላይ የተመሰረ የውሃ ምደባ ሰርዓት ለመገንባት ለባለድርሻ አካላት የሚዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የአዋሽ ተፋሰስ ለመስኖ፣ ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና ልማት የተሻለ እና ከሌሎች ተፋሰሶች ቀድሞ ወደ ልማት የገባ በመሆኑ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ውስጥ በመንግስት፣ በግል ባለሀብቶችና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የመስኖ ልማት የበለጠ የተስፋፋበት ነበር ብለዋል።

በተከዜ ተፋሰስ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ዕቅድ የባለድርሻ አካላት የግምገማ ዓውደጥናት እየተካሄደ ነው።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የውሃ ሀብት ተጠቃሚ የማድረግ፣ የማዳረስና የማስፋት ስራዎች እየተሰራ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑ ተገመገመ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የተነሱ ሀሳቦች ላይ በሚገባ ማየትና ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ገልጸው አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል

በኔፕ-አዴሌ ፕሮጀክት ትግበራ መመሪያ እና በአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር ስርአት ዙሪ ግንዛቤ መፍጠር የተሻለ አፈጻጸምን እንሚያመጣ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ትግበራን ለማሳለጥ ፕሮጀክቱን ለሚተገብሩ እና ለባለድርሻ አካላት የተለያዩ ቴክኒካል እና የአቅም ግንባታን ስራዎችን በማከናወን የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን ትግበራ ለማሳለጥ አቅምን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

Dec 2025

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የወዴቻ ንዑስ ተፋሰስ በባለድርሻ አካላት ተጎበኘ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል ጋር በጋራ በሚተገበረው የብሬይት ፕሮጀክት የወዴቻ ንዑስ ተፋሰስ ላይ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ የዳሰሳ ጥናት እና የ10 አመት እቅድ ተዘጋጅቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበታል።

በስድስት ከተሞች በሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት የትግበራ ሂደት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ምክክር ተካሄደ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ መንግስት ትኩረት የተሰጠው ከተሞችን የማልማትና አረንጓዴና ፅዱ አካባቢን ከመፍጠር ተልዕኮ ጋር የተሳሰረ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ከየቤቱ የሚወጣ ፍሳሽ ቆሻሻን በአግባቡ ለማስተዳደርና መልሶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚቻልበትን ሳይንሳዊ መንገድ በማመቻቸት የሚተገበር በመሆኑ ይህ

የዳሳሳ ጥናቱ ግኝትና ምክረ ሀሳብ መሬት ወርዶ ተግባራዊ ከሆነ የፕሮጀክቱ ዋና ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል /Water and Land Resource Cente WLRC/ ጋር በመተባበር በብራይት /BRIGHT/ ፕሮጀክት አመቻችነትና አሳላጭነት በኢንፍራንዝ ንዑስ-ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተፋሰስ ልማት ዕቅድ ላይ ለ3 ተከታታይ ቀናት ባህርዳር ከተማ ሲካሄድ የነበረ የባለድርሻ

ሰነዶቹ ለትግበራ በሚመችና በሀገራዊ የሪፎርም አቅጣጫ መሰረት በጥራት እየተዘጋጁ መሆኑ ተገለጸ።

በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎችን አስመልክቶ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ክፍል በቢሾፍቱ ሰራ አመራር ኢንስቲትዩት ተገኝቶ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስትራቴጅክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም የዋናው መስሪያ ቤት ቴክኒካል ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የዝ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታን ከሚሰሩ ውሃቢሮ ፣ አማካሪ ድርጂቶችና ኮንትራክተሮች ጋር ተወያዬ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል በመንግስት በጀት በሚደገፉ የCR-WaSH የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ከክልል ውሃቢሮ ፣ አማካሪ ድርጂቶችና ኮንትራክተሮች ጋር ውይይት ያደረጉት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደ

በአዋሽ ተፋሰስ የወዴቻ ንኡስ ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተፋሰስ አስተዳደር እቅድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል ጋር በጋራ የሚተገበረውና የብራት ፕሮጀክት አካል በሆነው በአዋሽ ተፋሰስ የወዴቻ ንኡስ ተፋሰስን ለማልማት በተካሄደው የዳሰሳ ጥናትና የአስተዳደር እቅድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

የኢንፍራንዝ ንዑስ-ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናት እና የተቀናጀ የተፋሰስ ዕቅድ ዓውደ-ጥናት እየተካሄደ ነው።

ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአሁኑ ወቅት በውሃ አስተዳደር ዘርፍ፣ በኢነርጂ ዘርፍና በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሰፊ ስራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን አንስተው የዕለቱ ዓውደ-ጥናት ቀጣይ በተፋሰሶች ላይ በተለይ በኢንፍራንዝ ንዑስ ተፋሰስ ላይና መሬት

በባዘርኔት ፕሮጀክት በአዋሽ ተፋሰስ ሊሰሩ በተመረጡ ሳይቶች ዙሪያ ጉብኝት መካሄዱ በቀጣይ ተግባራት ትልቅ ግብዓት ይሆናል-አቶ ሞላ ረዳ የባዘርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ

ከጉብኝቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአዋሽ ተፋሰስ ነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ውይይት የተደረገበት መሆኑን አስታውሰው ይህንን ውይይት ተከትሎም የተመረጡ ሳይቶች ጉብኝት እንዲካሄድ መደረጉን አስታውሰው የተመረጡ ሳይቶች ለተቀናጀ ውሃ ሃብት አስተዳደር ምቹ መሆናቸውን ለመ

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ ነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በያንጉዲ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እንሰራለን።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለደቡብ ሱዳን የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር ለመጡ ልዑካን የተዘጋጀው የልምድ ልውውጥ እና የአቅም ግንባታ ስልጠና ማጠቃለያ መርሀ ግብር ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ባደረጉት ንግግር ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እ

የዩኤን ዲፒ (UNDP)ስቲሪንግ ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይት አደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የዩኤንዲፒ/UNDP/አፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም እስቲሪንግ/String/ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች፣ በተዘረጉ አስቻይ ሁኔታዎች፣ በመጡ ለውጦችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይአድርጓል።

በጣም ገጠራማ ለሆኑ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሀይል ከሚያቀርቡ በዘርፍ ከተሰማሩ የ16 የግል ድርጅቶች ውል የማደስና ከ13 ተጨማሪ የግል ድርጅቶች ጋር ውል የመግባት ስነስርዓት ተካሄደ ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢትዮጵያ እምቅ የኢነርጂ ሀብት ያላት ሀገር እንደሆነና ከለውጡ ወዲህ እንደሀገር በዘርፉ ከፍተኛ ስራ ተሰርቶ ውጤት ምጣቱን ገልፀው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብና ቅንጅታዊ አሰራርን ይጠይቃል ብለዋል።

ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተገነባው የንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ውሃ ላይ ያሉ ትልቁ ስኬታችን ጉድጓድ ተቆፍሮ ውሃ ሲወጣ እና ፕሮጀክቱ ህይወት ዘርቶ ወደ ህብረተሰቡ ሲደርስ ነው በማለት የወረዳው ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከአጋር አካላት ጋር በጋራ መስራት የጎላ ሚና አለው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር Mr. Sune Krogstrup ጋር በከርሰምድር ውሃ ካርታ (ground water mapping) እና በአቅም ግንባታው ዘርፍ በትብብር ለመስራት በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃ ሀብት አስተዳደር ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የባዘርኔት ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል የቀላፎ ወረዳ አሎ አጋርሲ ተፋሰስ በተጎበኘበት ወቅት ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ከውሀ ሀብት እና ከመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበሩ ያሉ ስራዎችን ጎበኙ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ የውሀ ሀብት እና የመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካንን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋም የሆነውን የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንሰቲትዩት ፣የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የአቃቂ ፍሳሽ ማጣሪያ ማእከልንና የአዳማ ከተማ ውሃ አገልግሎትን ጎብኘተዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከስምንት አማካሪዎች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማስፋት በሚደረገው ጥረት እንደአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች ውስጥ በ55 ወረዳዎች በሚተገበሩ የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ስራዎች የአቅም ግንባታና ከግንባታ በኋላ የፕሮጀክቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ከአ

ለ22 ፕሮጀክቶች 26 እስታንድባይ ጀኔሬተሮች /standbygenerators/ የግዥ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት የሚገነቡ በአጠቃላይ በ55 ወረዳዎች 110 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንዳሉ ገልፀው ጀኔሬተሮቹ የሚገዛላቸው 22ቱ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙና በመጠናቀቅ ላይ የሉ ናቸው ብለዋል።

ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

የቪዥን አካዳሚ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጂታል ኤግዚቢሽኑን በጎበኙበት ወቅት ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

በሃዋሳ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት (Faecal Sludge and Septage Treatmenet Plant ) ግንባታና ጥገና የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ በ23 ከተሞች የሚተገበር የሁለተኛው የከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት አካል የሆነው በሃዋሳ ከተማ የሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ እና ማስወገጃ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከተሞችን ጽዱ፣ ማራኪ እና ውብ ለማድረግ እያከናወነ ያለ

ለሕዝባችን ሁለንተናዊ የውሃ አቅርቦትና የንፅህና አጠባበቅ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከገንዘብ ድጋፍ በላይ ውጤታማ አፈፃፀም በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ፒ..ኤች.ዲ) ባለፉት 3 ዓመታት የፕሮጀክቱን የአፈጻጸም ሂደት ለመገምገም እና በቀሪ ሦስት ዓመታት የፕሮጀክቱን ዓላማ ለማሳካት ለሚመጡት 3 ዓመታት የፕሮጀክት ትግበራ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መንግስትን እና ዓለም ባንክን የሚያጣምረው ይህ የግምገማ መድረክ ወሳኝ ምዕራፍ መሆ

በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ሲሉ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ''ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በተከበረበት ወቅት ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ብለዋል።

በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ ተግባራዊ ለሚደረገው የተቀናጀ ስራ ምቹ ሁኔታ መኖሩ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሰሞኑ በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ በባዘርኔት ፕሮጀክት ተግባራዊ የሚደረገውን የተቀናጀ ስራ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርትን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን ይህንን አስመልክቶ ለስራው የተመረጡ አካባቢዎች ተጎብኝተዋል።

ከ299 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የሲቪል ስራና የኤሌክትሮመካኒካል መስመር ዝርጋታ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የኢዋያ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቦረና አካባቢ እንደሚገኝ ገልፀው አካባቢው በከፍተኛ ሁኔታ ውሃ አጠርና ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በድርቅ የተጠቃ አካባቢ በመሆኑ ስራው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ በፍጥነትና በጥራት መሠራት አለበት ብለዋል።

ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ ቤቶች የቁሳቁስ የአቅም ግንባታ ድጋፍ ተደረገ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የቁሳቁስ ድጋፉ የተደረገው በ7 ክልሎች በ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ቤቶችን አቅም ለማጎልበት፣ አገልግሎቱን ለማዘመንና ለማሳለጥ እንደሚየግዝ ታስቦ ነው ብለዋል።

በ15 ሚሊዮን ብር የተቀናጀ የመረጃ ሲስተም ለማልማት ሶፍትዌር ከሚያለማ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃልማት ፈንድ ብድር አስተዳደር በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ደረጃውን በጠበቀ የመረጃ አያያዝ በአይቲ /Information Technology/ መደገፍና ሲስተሙ መዘርጋት ስላለበት የውልስምምነቱ አስፈልጓል ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ተግባር ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገለጹ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስና ለዘመናት የሀገር ዕድገት ማነቆ ሆኖ ቆይቷል፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ሰፊ ተግባር ውጤት መመዝገቡን ተናግረው ለዚህም ውጤት መመዝገብ በዋነኝነት የሚጠቀሠው የተቋማት አሠራር በሪፎርም እንዲቃኝ መደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት ተደረገ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ውሃን በተመለከተ በርካታ ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የውሃው ዘርፍ በራሱ ተደራጅቶ እንዲመራ መደረጉ ለውጤቱ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።

ከ48 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር የአቅም ግንባታ ስልጠና ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ በገጠርና በከተማ በተለያዩ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰራው የአቅም ግንባታ ስራ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለብዙ አመታት ያካበተውን አቅም በመጠቀም ብቃት ያላቸውን ባለሞያዎችን ለማፍራት ስት

Nov 2025

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ልማትፕሮጀክት የሩብ ዓመት የግምገማ ሪፖርት ቀረበ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ለማት ፕሮጀክት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች በተደጋጋሚ ከሚጠቁ አምስት የአፍሪካ አገራት የመጠጥ ውሃ እና መስኖ ልማት ዋነኛ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ አካባቢያዊ እና ማህበራዊ የል

የውሃ ሀብት አጠቃቀምንና ፈቀቃድ አሰጣጥን ማዘመን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክልል ውሃ ቢሮዎች፣ ከቤዚን አስተዳደር ፅ/ቤቶች፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤት እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች ተወክለው ከመጡ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የውሃ ሀብት አጠቃቀምና ፈቃድ አሰጣጥን ማዘመንና /E-Service/ አሰጣጥ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።

በክትትልና ግምገማ እና የመማማር ማዕቀፍ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፕሮጀክቶች ሳይት ዙሪያ ድጋፍና ክትትል በሚደረግበት ወቅት ኮንትራክተሮች ምን እንደሚሰሩ በጥልቀት መመርመር፣ አማካሪዎች ሚናቸውን በአግባቡ መወጣታቸውን መቃኘትና የመስሪያ ቤቱን አቅርቦት መፈተሽ ይገባል ያሉ ሲሆን እስከ ነሀሴ ወር መጨረሻ እያንዳንዱ ፕሮጀክት ያከናወናቸውን ተግባራት

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለው ለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጎበኘ።

በውሃ ልማት ፈንድ እያስገነባቸው ከሚገኙት የመካከለኛ ከተሞች መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እና ከ5000ሜትር ኩዩብ ውሃ የማጠራቀም አቅም ያለውን የለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ያስጎበኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች ፕሮጀክቶቹ በተሻለ

ከ839 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት አለኝታ ልየታና ልማት የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ፕሮጀክቱ የምስራቅ አፍሪካ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል ሲሆን በ240 ቀናት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ገልጸዋል፡፡

ወደ ሪፎርም መግባት ጊዜው የሚጠይቀው ተግባር መሆኑ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ሀገር በሁለተኛው ዙር ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት አንዱ መሆኑን የገለጹት አቶ ማሙሻ ሪፎርሙን በውጤታማነት ለመፈጸም በየደረጃው አብይ ፣ ቴክኒካል እና ንኡሳን ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ተግባር ተገብቶ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የድጅታል አሰራር ስርዓቱ የተለየ ተነሻሽነት ፈጥሯል ሲሉ የናይጄሪያ ቡድን አባላት ተናገሩ።

ባለሞያዎቹ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የመጡ ሲሆን በነበረው ውይይት በውሃ ሀብት አስተዳደር፣ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እና በኢነርጂ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከተለያዩ ለጋሽ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

ክቡር አምባሳደር በውይይቱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰረተ ልማት ግንባታ እና ዘለቄታዊ አገልግሎትን አስመልክቶ ከጤና፣ ከትምህርትና ከገንዘብ ሚኒስቴር መ/ቤቶች ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሆነ ገልፀው፤ በአሀዳዊ ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰ