በልማት ስራዎች ጉብኝት፣በ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና በተለያዩ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ሲካሄድ የነበረ መርሃግብር ዛሬ ተጠቃለለ።
ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የሁሉም ክልል የውሃና ኢነርጂ ቢሮ የ6ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መቅረቡ አንዱ ክልል ከሌላው ክልል መልካምና ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ልምድ በመለዋወጥ ሁሉም ወደተሻለ አፈፃፀም ደረጃ እንዲደርስ ስለሚያግዝ ነው ብለዋል።