Apr 2025

የፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን በማዘመን ውብ ፣ ፅዱና ምቹ ከተማ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተባባሪ አቶ ሙሴ ገ/ስላሴ እንዳሉት 26 የህዝብ እና 14 የጋራ ዘመናዊና ደረጃቸውን የጠበቁ መፀዳጃና ገላ መታጠቢያ ቤቶች እንደተገነቡ ገልፀው በተደራጁ ማህበራት አማካኝነት የገቢ መሰብሰብና የቁጥጥሩ ስራው በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የብሄራዊ የመጠጥ ውሃ፣ የሳኒቴሽን እና የኃይጅን (one wash) ፕሮግራም አፈፃፀም ተገመገመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ባለፉት ዓመታት ንፁህ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ከክልሎች እና ከፌዴራል ዋን ዋሽ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ተጨባጭ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው የአገልግሎት መቆራረጥጦች በኃይል አቅርቦትና የጥጋና ማዕከላት ውስንነቶች ምክንያት የሚፈጠሩ በመሆኑ በዘላቂነ

ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የሆራ-አዘብ ከተማ የባለብዙ መንደር የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ከ300 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደተገነባ ገልጸው ፕሮጀክቱ የቢሮ ግንባታ ፣ የተሽከርካሪ እና ሌሎች ግብአቶች የተሟሉለት በመሆኑ ቀሪውን ስራ ክልሉ በማስተዳደር በተለይም የውሃ ክፍያ ስርዓትን በመዘርጋት ስራው እንዲቀጥል በማድረግ እና የአገልግሎት አሰጣጡ

የውሃ ሀብት ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን ለመቋቋም ውሃን ማእከል ያደረገ የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት የቤዝን እቅድ መተግበር እንደሚገባ ተጠቆመ።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ውሃን ማዕከል ያደረገ የተቀናጀ ባለድርሻ አካላት የቤዚን እቅድ፣ የተፋሰስና የውሃ አካላት ጥበቃ፣ አሳታፊና ፍትሃዊ የውሃ ሀብት ምደባና አጠቃቀም ፈቃድ ስርዓት፣ ዘመናዊ የመረጃ ስርዓት፣ ውጤታማ የባለድርሻ አካላት ትስስር መፍጠርን በውሃ ሀብታችን ዙሪያ የሚታዩትን ተግዳሮቶች እልባት ለመስጠ

ባለፋት ዘጠኝ ወራት ያስመዘገብናቸው ድሎች ሁሉ በዘርፋ ያሉ ችግሮችን እንደሚቀንሱ ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በጋራ በመሆን በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ በውይይት ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ሀሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ እና የዘርፎች እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ውይይት ተደረገ።

የማክሮ የኢኮኖሚ እና የዘርፎች የ9ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደሀገር ኢትዮጵያ ያለችበት ደረጃ ምን ይመስላል፣ ምን አሳክተናል፣ ማሻሻያዎቹስ ምን ለውጥ አመጡ የሚለውን በጋራ ለመገምገም ያለመ መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዋቢሸበሌ ቤዝን የሚተገበረው የቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት (BaSRINET) ማስጀመሪያ መርሃግብር በጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ፕሮጀክቱ በብሔራዊ የተቀናጀ ውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም ከታቀፉ ፕሮጀክቶች ውስጥ አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዋናነት በዋቢ ሸበሌ ቤዚን የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ማህበረሰቦችን በሚደግፍ መልኩ እንደሚተገበር ጠቁመዋል፡፡

የቶጎጫሌ ከተማ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት በቃ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በበኩላቸው የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ ማጠናቀቅ መሠረታዊ ቢሆንም ዘላቂነቱን የሚያረጋግጡ ስራዎች ካልተሰሩ ተገቢውን ግልጋሎት ማግኘት አይቻልም ያሉ ሲሆን፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ፕሮጀክቱ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና አገልግሎቱ እንዲሳለጥ የውሃ አገልግሎት ተቋሙን የማ

ስለውሃ ጥራት የሚቆጭ፣ የሚቆረቆር፣ ዕሴት የሚጨምርና ሰፊ ዕይታ ያለው ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ስልጠናውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ የሀዋሳ ሀይቅ ብዙ ጫና ያለበት በመሆኑ የውሃ ጥራት ቁጥጥር ስራውን ለማገዝ የአካባቢው በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን በመጠቀም ብቸኛ አማራጭ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስርዓት እንዲሰፍን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማእከል ጋር በጋራ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስርዓትን ለማስፈን ተግባራዊ ከሚደረጉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነውን የብራይት ፕሮጀክት በአምስት ዋና ዋና ተፋሰሶች በአባይ ፣ አዋሽ ፣ ኦሞጊቤ ፣ተከዜና ስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰሶች ላይ እየተገበረ ይገኛል።

የብራይት ፕሮጀክት በስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስ በይፉ ወደ ተግባር ሊገባ ነው።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለውና ውስብስብ ችግሮቾ ያሉበትን የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስ በተቀናጀ መልኩ ለመምራት ፣ለማስተዳደርና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር አካል በሆነው የብራይት ፕሮጀክት ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

በማህበረሰብ አቀፍ የውሃ ጥራት ክትትል ስራ (Citizen Science) ፅንሰ ሀሳብ ላይ ተግባር ተኮር ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ሳይንስን የሚደግፉ ፍቃደኛ ዜጎችን በማስተባበር የውሃችንን ጤንነት ለመጠበቅ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት በመሆኑ ፍቃደኛ ወጣቶችን በማሰልጠን ወደ ስራ ለማስገባት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ ከአፍሪካ ግሪን ሀይድሮጅን ፓርትነርሺፕ አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ ግሪን ሀይድሮጅን ላይ ለመስራት አስቻይ ሁኔታዎች መኖራቸውን አንስተው፤ የአፍሪካ ግሪን ሀድሮጅን ፓርትነርሽፕ ለሚያደርጋቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡

ከ20 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የክትትል ፣ቁጥጥርና የኮንትራት አስተዳደር ውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በዋን ዋሽ ፕሮግራም ሲአር ዋሽ ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አካል የሆነው በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት 37 ሺ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የአዩን የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክትን የክትትል፣ ቁጥጥርና የኮንትራት አስተዳደር ስራ እንዲያከናዉኑ ከሶማሌ

በ25 ሚሊየን 732 ሺ 4 መቶ ብር በሚሆን ወጭ የክትትል፣ ቁጥጥርና የኮንትራት አስተዳደር ውል ስምምነት ተፈረመ::

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በዋን ዋሽ ፕሮግራም ሲአር ዋሽ ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የጉራዳሞሌ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በሚፈለገው ደረጃ በጥራትና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ተገንብቶ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲፈታ የተደረገ የውል ስምምነት ነው ብለዋል፡

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሰደር ሱን ክሮግስትሩፕ ጋር በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ትብብር ዙሪያ በአቅም ግንባታ፣ በቴክንካዊ ድጋፍ እና በታዳሽ ኢነርጂ ልማት ኢንቨስትመንት ላይ፤ በተለይም በንፋስ ኃይል ልማት ላይ በትብብር እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ በመጠጥ ውሃ ዘርፍ፤ በተለይ

በሶስቱ ተፋሰሶች የሚተገበረው የብራይት ፕሮጀክት በሙሉ አቅም ወደ ተግባር ሊገባ ነው።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የብራይት ፕሮጀክት በሀገር ደረጃ የተዘጋጀውን የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር እቅድ በሚገባ ወደ መሬት ለማውረድ የሚያስችለው ብራይት ፕሮጀክት በ11ክልሎች በአምስት ተፋሰሶች በአባይ ፣ አዋሽ ፣ ተከዜ፣ ኦሞ ጊቤና ስምጥ ሸለቆ ተፋሰሶች ላይ ያለውን የውሃ መጠንን፣ ጥራትን እና አጠቃላይ የ

በጣም ገጠራማ አካባቢዎች ላይ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመተባበር በቡብ ምእራብ ዞን ሚኒት ሸሽ ወረዳ ይርን ቀበሌ የተገነባ የሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት በተመረቀበት ወቅት በጣም ገጠራማ አካባቢዎች ላይ የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።

በ60 ሚልዮን ብር ወጪ የተገነባው የሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በስፍራው ተገኝተው የፕሮጀክቱን ስራ መጀመር ባበሰሩበት ወቅት በኢትዮጵያ መንግስት፣ ከዓለም ባንክ እና ከሌሎች የፋይናንስ ምንጭ የሚደገፈው የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም አካል በሆነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክና መብራት ተደራሽነት/Access to distributed Electricity

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የተመራ ከፍተኛ አመራር በጅማ ዞን ጌራ ወረዳና በሻሻ ቀበሌ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሄዱ።

የብዙ አመታት የመልካም አስተዳደር ችግሮች በተለይም የአጋሮ በሻሻ እና ጌራ ኤሌክትሪክ መስመር ችግር በአዲስ መልክ ለመዘርጋትና ጥገና ለማካሄድ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኩል ስራው እንደተጀመረ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ ገልፀው፤ የቆዩ የህብረተሰብ ቅሬታዎችን ለመመለስ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኩል እንደ

የአሞኒያ ማዳበሪያ በሀገር ውስጥ ለማምረት የሚደረገውን ጥረት አጋዥ የሆነ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከጂአይዜድ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በተዘጋጀው የስልጠና መድረክ ያነጋገርናቸው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ሀብት ጥናት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ካሌብ ታደሰ ስልጠናው በሶስት ዙር የተሰጠ ሲሆን እንደሀገር የግሪን ሀይድሮጅን ቴክኖሎጅን በመጠቀም የአሞኒያ ማዳበሪያ በማምረት በምግብ ራሳች

የሚታዩ ክፍተቶች ቀጣይነት ባለው አቅም ግንባታ ስራ በመፍታት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

በአደሌ ፕሮጀክት አተገባበር ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ላይ በቀረበው ሰነድ ላይ በተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚነስትር ዲኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በሰጡት ማጠቃለያ ላይ የሚታዩ ክፍተቶች ቀጣይነት ባለው አቅም ግንባታ ስራ በመፍታት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ በቁርጠ

የምስራቅ ድል አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጅታል ኤግዚቢሽን ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በማዕከሉ በነበራቸው ቆይታ እንደ ሀገር ያለንን የከርሰምድርና የገጸ ምድር የውሃ ሀብት አጠቃቀም ፣ አያያዝ እና ህዳሴ ግድብን በሚመለከት በባለሙያ በስፋት ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን በተለይም ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከተማሪዎቹ ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

በኔፕ-አዴሌ ፕሮጀክት ትግበራ መመሪያ እና በአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር ስርአት ዙሪያ ለባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ተጀመረ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ትግበራን ለማሳለጥ ፕሮጀክቱን ለሚተገብሩ እና ለባለድርሻ አካላት የተለያዩ ቴክኒካል እና የአቅም ግንባታን ስራዎችን በማከናወን የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን ትግበራ ለማሳለጥ አቅምን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ ስልጠና

በአለም ባንክ ልዑካን ቡድን የመስክ ጉብኝት ተካሄደ።

የአለም ባንክ ልዑካን ቡድን ከኢትዮጲያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት አስተባበሪዎች ጋር በመሆን በ2016 በጀት ዓመት በታችኛው አዋሽ ተፋሰስ በአይሰኢታ እና አፋምቦ ወረዳዎች ላይ የተሰሩ የጎርፍ መከላከል ስራዎች ላይ የመስክ ጉብኝት አደረጉ።

ከ224 ሚሊየን 784 ሺ ብር በላይ በሚሆን ወጭ የመጠጥ ውሃ ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃ እና በተቀመጠው ጊዜ ፕሮጀክቱን ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ያሉንን በረከቶች አውጥተን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ "ትላንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ያሉንን በረከቶች አውጥተን በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

"ትላንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል ውይይት እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ "የመጋቢት 24 ፍሬዎች እና ቀጣይ የሀገራችን ተስፋ" በሚል የተዘጋጀ ፅሁፍ ለውይይት ባቀረቡበት ወቅት የዛሬ ሰባት አመት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትራችን ኢትዮጵያውያን ያነሱትን ጥያቄ ተቀብለው በራሳቸው ፍቃድና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ህዝቡ ወዶና ፈቅዶ በመረጠው እንድትመራ ስልጣን ያስረ

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የተገነቡና በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡና በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ጥሩ አፈጻጸም የታየባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

Mar 2025

በቦረና ዞን የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል ከሆኑት ፕሮጀክቶች መካከል 100 ኩዩቢክ ሜትር ሪዘርቬየር ያለው የሮምሶ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከ106 ሚሊየን 300

በሞዮ ወረዳ የሜጢ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ፕሮጀክት አካል የሆነው በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በሞዮ ወረዳ የሚጤ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ቀድሞ አገልግሎት መስጠቱ ታውቋል።

በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ጉጂ ዞን የፊንጫዋ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ የከፍተኛ አመራሮች ቡድን በምእራብ ጉጂ ዞን ፊንጫዋ ከተማ በመገኘት የፊንጫዋ ከተማ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የደረሰበትን አፈጻጸም ገምግመዋል።

ክቡር ሚኒትሩ ከአልጀሪያ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእረግ የኢነርጂ፣ ማእድንና ታዳሽ ኢነርጂ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያና በአልጀርያ መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳለ ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በምሰራቅ አፍሪካ የሀይል ትስስር እንዲፈጠር በማድረግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተች መሆኑን ጠቁመው፤ ኢነርጂ ላይ የሚሰሩ የአልጀሪያ ካምፓኒዎች በኢትዮጵያ የሀይል ልማት ዘርፍ ላይ መሳተፍ

የውሃ ሀብታችንን በመጠበቅ ፣ በመንከባከብ እና በማልማት ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚጠበቅ ተገለጸ።

በአሉን አስመልክቶ በነበረው የፖናል ውይይት የዘርፉ ምሁራን እንዳሉት የውሃ ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የምንተክላቸው ዛፎች በተለይም በተፋሰሶች አካባቢ የሚተከሉት ውሃን በብዛት የሚጠቀሙ እንዳይሆኑ ባለፉት ስድስት አመታት የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራዎቻችን ላይ ተግባራዊ ተደርጓል ብለዋል።

''የውሃ ጥበቃን መረዳትና ማጎልበት" በሚል መሪ ቃል የአለም ውሃ ቀን እየተከበረ ነው።

በአለም አቀፍ ደረጃ ማርች 22 በኢትዮጵያ ደግሞ መጋቢት 13 የሚከበረው የአለም የውሃ ቀንን ስናከብር ውሃ ሀብትን በተመለከተ ልንገነዘባቸውና ትኩረት ልናደርግባቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች አሉ ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተናግረዋል። አክለውም

ለኦሞ ጊቤ ቤዚን ፕላን ተግባራዊነት ቤዚኑን የሚጋሩ ክልሎችና ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ።

የኦሞ ጊቤ ቤዚን ይፋዊ ማስጀመሪያ መድረኩን የመሩት የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ በቀጣይ አምስት አመታት የሚተገበረው ፕሮጀክት በተናጠል የሚመራ ከሆነ የፍትሃዊነት ችግርን ስለማይፈታ በቀጣይ ከውሃ ሀብት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የሚሰሩ ተቋማትን አቅም በማጎልበት ዕቅዳቸውን

8 ሚሊዬን ብር የሚያወጣ የየቤተሙከራ ልቀት መጠን መለኪያና መቆጣጠሪያ ማሽን/Laboratory Emission Monitoring System/LEMS/ ርክክብ ተደረገ።

የገጠር ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ ወልዱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢነርጂ ዘርፍ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ገልፀው፤ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ በሚውል የቤተሙከራ የልቀት መጠን መለኪያና መቆጣጠሪያ ማሽን /Laborat

በ ብራይት (BRIGHT) ፕሮጀክትን በኦሞ ጊቤ ቤዚን ለማስጀመር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ሚኒስቴር መ/ቤቱ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን እውን ለማድረግ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ብራይት (BRIGHT) ፕሮጀክት በተመረጡት አምስቱ ቤዚኖች ላይ ማለትም አባይ፣ አዋሽ፣ ኦሞ-ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ ሀይቆች እና የተከዜ ቤዚኖች ላይ የተሻለ የውሃ አጠቃቀምን ለማስፈን የቤዚን

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የኢፍጣር ፕሮግራም አካሄደ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የረመዳን ፆምን ምክንያት በማድረግ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የበላይ አመራሮች በተገኙበት ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች ጋር የአፍጥር ስነስርዓት ተካሂዷል።

ክቡር ሚኒትሩ ከፊላንድ ልኡካን ቡድን ጋር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፊንላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ፣ የመካለኛው ምስራቅና የላቲን ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር በአምባሳደር ሄሌና ኤራክሲነን ከተመራ የፊላንድ ልኡካን ቡድን ጋር በውሃው ዘርፍ በሚያደርጉት ትብብር ላይ ትኩረት አድርጎ በተካሄደው ውይይት ላይ ክቡር ሚኒስትሩ የፊላንድ መንግስትና

የባዘርኔት ፕሮጀክትን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ሀይድሮሎጅካል ሞዴሊግ ተግባራዊ ሊሆን ነው።

በCIMA (ሲማ) ፋውንዴሽን የምርምር ድርጅት ተዘጋጅቶ የቀረበው የሀይድሮሎጅካል ሞዴሊግ ሲስተም በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚሰራው ስራ የተሳለጠ እንዲሆን ያስችላል ሲሉ የአውሮፖ ህብረት ፕሮግራም ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ማርኮ ላንዲ በሲምፖዚየሙ መክፈቻ ላይ ገልጸዋል። ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በተለያዩ ፕሮጀ

በሚቀጥሉት ስድስት ወራት የህዳሴ ግድብ ሪቫን እንቆርጣለን ሲሉ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ ገለጹ።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ በሚቀጥሉት ስድስት ወራት የህዳሴ ግድብ ሪቫን እንቆርጣለን;; ህዳሴ ግድብን ብዙ ዋጋ ከፍለንበታል ያሉት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአንድ ብር እርዳታም ሆነ ብድር ከውጭ ያልተገኘበት ፣ብዙ ፈተና ያየንበ

ኢትዮጵያ ለጋምቢያ በታለቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ልምድ አካፈለች፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተሞክሮ ላይ ትኩረት አድርጎ በተካሄደው ውይይት ኢትዮጵያ ሀይል ከውሃ የማመንጨት የዳበረ ተሞክሮ እንዳላት አንስተው፤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአፍሪካ በትልቅነቱም ሆነ፤ በፋይናንስ ምንጭና ከህዝባዊ ተሳትፎ አንጻር በርካታ ተሞክሮዎች የተገኘበት

በግድብ ደህንነት ጋይድላይንና አተገባበር ዙሪያ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ስልጠናውን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ የግድብ ባለቤት ሆነው ግድብ አስተዳደር ላይ የሚሰሩ፣ ግድብ ኦፕሬት የሚያደርጉና የግድብ ደህነንትን ለሚጠብቁ ሶስቱ አካላት በተዘጋጀው የግድብ ደህንነት ጋይድላይንና አተገባበር ዙሪያ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ

የውሃ ሀብት አስተዳደር ስርዓትን ለማስፈን የሚያስችሉ የህግ ማእቀፎች መዘጋጀታቸው ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ በሃገር የውሃ ሀብት አስተዳደር ስርዓትን ለማስፈን የሚያስችሉ የህግ ማእቀፎች መዘጋጀታቸው ኢትዮጵያ እንደ ሀገር በቂ የዝናብ መጠን፤ በርካታ ወንዞችና ሀይቆች እዲሁም ሌሎች የውሃ አካላት ቢኖሯትም የዝናብ መጠኑ በቦታና በጊዜ ያለው ስርጭት የተዛባ በመሆኑ፤ በተፈጥሮ ሀብት መራቆት፤ በአየር

የዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጂታል ኤግዝቢሽን ማእከልን ጎበኙ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተግባርና ሃላፊነት ዙሪያ ገለጻ ለተማሪዎቹ ያደረጉ ሲሆን፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በተለይ ከ2014 ዓ.ም. ጀምሮ እንደ አዲስ ሲደራጅ በሶስት መሰረታዊ ዘርፎች፤ ማለትም የውሃ ሀብት አስተዳደር፣ የመጠጥ ውሃ ሳኒቴሽን እንዲሁም

ከ344 ሚሊዬን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚገነባ የባለ ብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው የውሃ ሽፋን ከክልል ክልል፤ ከአካባቢ አካባቢ ወጥነት እንደሌለው አንስተው፤ በተለይ ውሃ አጠርና ድርቅ የሚያጠቃቸው አካባቢዎችን ታሳቢ በማድረግ የባለብዙ መንደር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ፕሮጀክት መተግበር መጀመሩንና የአዩን የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክትም የፕሮጀክቱ አካል

የቶጎጫሌ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 97 ከመቶ መጠናቀቁ ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኢ/ር ዶክተር ሀብታሙ ኢተፋ፣ የውሀና ኢነርጂ ሚኒስትር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ፣ የሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር መሀመድ ሻሌን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ አመራሮች ዛሬ የግንባታውን ሂደትና የሙከራ ስርጭት ተዟዙረው ተመልክተዋል።