Jun 2025

ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የኤሌክትሮመካኒካል ዕቃ አቅርቦትና ዝርጋታ ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲኔጋሞ የፕሮጀክቱ ሲቪል ግንባታ ስራው እየተፋጠነ እንደሆነ አንስተው የኤሌክትሮመካኒካል የዕቃ አቅርቦትና የዝርጋታ ስራውን ያሸነፈው ድርጅት ከዚህ ቀደም ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በነበረው የስራ ውል ጥሩ አፈፃፀም እንደነበረው ገልፀው አሁንም የበለጠ አፈፃፀም በማሳየት በታቀደው ጊዜ

ከ2 ሺ 500 በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመተሃር ሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን በፍትኃዊነት ለሁሉም ማህብረሰብ እንዲዳረስ የመከታተልና የመተግበር ኃላፊነት ያለው መሆኑን ገልጸው በሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክቶች፣ በትምህርት እና በጤና ተቋማት የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮጀክቶችን እንዲሁም በቤ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት አለሚቱ ኡሞድ ጋር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የህብረተሰቡን የሀይል ተደራሽነት ለማስፋት ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ በርካታ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ጠቁመው በዚሁ ክልልም ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀው ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ የሶላር ግሪዶችን እንየገነባ ሲሆን የሶስት ወረዳዎች የሶላር

የንጹህ ማብሰያ ፍኖተ ካርታው የምግብ ማብሰል ሂደቱን ጤናማ ከማድረግ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተገለጸ፡፡

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ፍኖተ ካርታው የሥርዓተ-ፆታ እኩልነትን ያካተተ በመሆኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶችን በንፁህ የምግብ አሰራር የእሴት ሰንሰለት ለማብቃት ያለመና በሴቶች ለሚመሩ ኢንተርፕራይዞችም በአቅርቦት ሰንሰለት፣ ስርጭት እና አገልግሎት ላይ ትልቅ ሚና እንዳው ገልጸዋል።

በአረንጓዴ ሀይድሮጅንና በባዮፊዩል ልማት ስትራቴጂ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ኢትዮጵያ ሰፊ ባዮማስ ያላት ሀገር በመሆኗ ግሪን ሀይድሮጅንን በማምረት ታዳሽ ኢነርጂዎች ጥቅም ላይ እንደሚውሉ የገለፁት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው፤ የከርሰምድርና ገፀ ምድር የውሃ ሀብቷን፣ የፀሀይ ሀይል፣ የጂኦተርማልና የነፋስ ሀይልን በመጠቀ

በአዋሽ ወንዝና በስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ዙሪያ በዘንድሮ በጀት ዓመት በተጀመሩ የጎርፍ መከላከል ስራዎች ላይ ክቡር ሚኒስቴሩ በተገኙበት ከአማካሪዎችና ከተቋራጮች ጋር ውይይት ተካሄደ።

በቀረበው ጽሁፍ ላይም ተቋራጮች ያለውን ምቹ ሁኔታና ተግዳሮቶች አንስተው በቀረቡት በነጥቦች ላይ በተደረገ ውይይትም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በአንዳንድ ቦታዎች ትኩረት መደረግ እንዳለበት አንስተው፤ በተለይ እስካሁን ያለው አፈጻጸም አጥጋቢ ባለመሆኑ ስራው ከመደበኛ ስራ በተለ

በከርሰ ምድር ውሃ ምርምር፣ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እና ማገገም (Rehabilitation) ምህድስና ላይ ያተኮረ አለም አቀፍ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከሱዳን የመጡ ሰልጠኞችን እንኳን ዳህና መጣችሁ ካሉ በኋላ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንሰቲትዩት ከስልጠና በሻገር የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ራዕይ እውን በማድረግ በውሃ ሴክተር ተጨባጭ መፍትሔ የሚያመጣ የፓሊሲ እና የፈጠራ ሀሳብ ማመ

የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምእራፍ የመስክ ሪፖርት ግኝት ላይ ውውይት ተደረገ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ቡድኑ ፕሮጀክቶቹ በሚገኙበት በሁሉም ክልሎች አንድ ወረዳና አንድ ከተማ በቦታው ተገኝተው ስራው ያለበትን ደረጃ በመገምገም በጥንካሬና በድክመት ለይተው ማቅረባቸው ሊያስመሠግናቸው ይገባል ብለዋል።

የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግርን በመፍታት ሀገራችን ለወር አበባ ንፅህና አጠባበቅ ተደራሽ እንድትሆን መስራት ይገባል ተባለ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከጤና ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ለ12ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ለ9ኛ ጊዜ "ለወር አበባ ንፅህና ተደራሽ የሆነ ሀገርን በጋራ እናረጋግጥ!" በሚል መሪ ቃል የሚከበረው የወር አበባ ጤናና ንፅህና አጠባበቅ አመታዊ ክብር በዓል ላይ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግርን በመፍታት

7.3 ሚሊዬን ብር በሚጠጋ ወጪ ባለ ብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የግንባታ ቁጥጥር እና የማማከር ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

የውል ስምምነቱን የተፈራረሙት የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በመጠጥ ውሃ ስራ የዲዛይንና የግንባታ ምዕራፍ ዋነኛውና መሰረታዊ ጉዳይ በመሆኑና የአካባበቢውን ማህበረሰብ በአጭር ጊዜ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ በከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ በመተግበር በታቀደው ጊዜ፣

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሙስናንና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ረገድ አርዓያ የሚሆኑ ስራዎችን መስራቱ ተገለጸ።

ጸረ ሙስና ኮሚሽን ያቋቋማቸው የሱፐር ቪዥን ቡድን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል አርዓያ የሚሆኑ ስራዎችን መስራቱን ገልጸው; ቡድኑ በሚኒስትሪው የተከናወኑ ስራዎችን ከተመለከተ በኋላ ከክቡር ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በኤግዝቢሽኑ ሀገራችን ያለችበትን የእድገት ደረጃ አይተንበታል፡፡

በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ለእይታ በቀረበው የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽንን እየተመለከቱ ያገኘናቸውና ነዋሪነታቸው በአሜሪካ የሆነው አቶ እውነት ላቀው ቤተሰባቸውን ይዘው ለጉብኝት የመጡ መሆናቸውን ገልጸው በጣም ዘመናዊ የሆኑ ቴክኖሎጂ ዎችን በመጠቀም የተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ሀገራችን ያለችበትን የእድገት ደረጃ በሚገባ

በኢትዮጵያ የገጸ ምድር ውሃ አካላት ጥበቃ፣ ማገገሚያ እና የመልሶ ማቋቋም ረቂቅ መመሪያ ላይ ምክክር እየተደረገ ነው።

መድረኩ ላይ የተገኙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዲኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ የውሃ ግኝትን አስተማማኝ ከማድረግ አንጻር እጅግ አሰፈላጊ የሆነውን የውሃ አካላት ጥበቃና መልሶ ማከም ስራዎችን ለማገዝ የሚያስችል የውሃ አካላት ጥበቃ ጋድላይን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከጂ.አይ.ዜድ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከዋተር ኤድ (Water Aid) ሉኡካን ጋር ተወያዩ።

ክቡር አምባሳደሩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ፣ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እንዲሁም በኢነርጂ ልማት ዘርፉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ላለፉት አራት ዓመታት በተሠራው ስራ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን 72 በመቶ ማድረስ መቻሉና በሀይል አቅርቦቱም ከ60በመቶ ያልበለጡ ኢትዮጵያውያንን ተደራሽ ማድረግ

አደሌ አና ኢሊፕ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን የሀይል ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሚናቸው የላቀ ነው ተባለ።

በድሬዳዋ ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ በቆየው የውይይት መድረክ ላይ የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ከዋናው የሀይል መስመር ርቀው የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በአደሌ አና ኢሊፕ ፕሮጀክቶች የሀይል ተጠቃሚ ለማድርግ በርካታ ስራዎች መሠራታቸውን አብራርተዋል።

የተደበቀው ሀይል (The hidden power) በሚል ርዕስ በሳይንስ ሙዚየም የተገነባው የውሃና ኢነርጂ ቋሚ ኤግዚቢሽን ሀገራችን ለመለወጥ ያለውን እምቅ አቅም ያሳያል ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ኤግዚቢሽኑ እንደ ሀገር ያሉን የውሃና ኢነርጂ እምቅ ሀብቶቻችን ሀገራችን ለመለወጥ ያላቸውን አቅም በተለይም ለታዳጊ ህጻናት በማሳየት ከወዲሁ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል።

የአዴሌ ፕሮጀክት ትግበራ፣ መመሪያና በአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር ስርአት ዙሪያ ከሚመለከታችው ባለድርሻዎች ጋር ውይይት እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ትግበራን የመምራትና የማስተባበር ሃላፊነትን በሚገባ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በኢሊፕ ፕሮግራም ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ተጠቃሚዎችን የማገናኘት ስራ እና በአደሌ ፕሮጀክት ደግሞ በጣም

ፕሮጀክቱ ኢነርጂ ማመንጨት ብቻ ሳይሆን ማስተማሪያም ጭምር መሆኑ ተገለጸ።

ፕሮጀክቱ በይፋ ስራ በጀመረበት እለት ከሚዲያ ጋር ቆይታ ያደረጉት በውሃ ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ሶላር ሚኒ ግሪዶችን በጣም ገጠርማ ለሆኑ አካባቢዎችና ለተለያዩ ተቋማት ከዚህ በፊት ስንጠቀምበት ቆይተን ሶላር ማቀዝቀዣዎችን እና ሶላር መስኖ ፖምፖችን በተለ

የውሃ አገልግሎቶች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት አደረጃጀት መገንባቱ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ አይነተኛ ሚና አለው ተባለ።

የውሃ አገልግሎቶችን አቅም ለማሳደግ የከተሞች ውሃና ሳኒቴሽን ፌደሬሽን ከዩኒሴፍ ጋር አዘጋጅተውት ለ5 ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ በቆየው ስልጠና ያነጋገርናቸው የፌደሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙክታር አህመድ በቂ፣ ዘላቂ ፣ጥራት ያለው ፣ የዘመነና የደንበኞችን ፍላጎት ያረጋገጠ የውሃ አገልግሎት ለመገንባት የተፈጠረው አደረ

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ግቢ ውስጥ 100 ኪሎ ዋት የሚያመነጭ የሶላር ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ተቋሙ በሶስት ዘርፎች ላይ በርካታ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በኢነርጂው ዘርፍ እንደሀገር 6.8 ጊ.ዋ ተደራሽ ማድረግናል ከሶላር ኢነርጂ 10 ሺ የሚጠጉ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መደረጋቸውን የጠቀሱት ክቡር ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የኢንተርናሽና

ከ110 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ልማት ፈንድ የተሻሻለ የንጽህና አጠባበቅ አገልግሎት መስጫ ፕሮጀክት አካል የሆነው ለ6 ከተሞች ለኮንስትራክሽን ቁጥጥር፣ የኮንትራት አስተዳደርና የአቅም ግንባታ ስራዎችን ለማከናወን SWS እና SRL አማካሪ ከመታፈሪያ አማካሪ ድርጅት ጋር በጋራ ከ110 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጭ የ

ከ331 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ።

ስምምነቱን የተፈራረሙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እ

የራሳቸውን አቅም እያጎለበቱ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የውሃ አገልግሎቶች እየተገነቡ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የውሃ አገልግሎቶች በፋይናንስ ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ፣ የዘመነ ቴክኖሎጅ በመጠቀምና የተሻለ የሰው ሀይል በማልማት የበቁ የውሃ አገልግሎቶች ሌሎችን እያገዙ እንዲያበቁ የማድረግ አሰራር ተዘርግቶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በውሃ እና ኢነርጂ ረቂቅ የፖሊሲ ሰነዶች ላይ ማጠቃለያ ውይይት ተደረገ ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በተሻሻሉት ረቂቅ የውሃ እና ኢነርጂ ማጠቃለያ ፖሊሲዎች ላይ የማኔጅመንት አባላትን በመጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን፣ በኢነርጂ ልማት እንዲሁም የሁሉም የጀርባ አጥንት በሆነው የውሃ ሀብት አስተዳደር ላይ በተዘጋው የውሃና ኢነርጂ ረቂቅ ፖሊሲዎች ዙሪያ ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ተደርጎ በ

የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምዕራፍ የስድስት ወር የመስክ ሱፐርቪዥን በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡

የሱፐርቪዥን ስምሪት ቅድመ ዝግጅቱን አስመልክቶ በተካሄደ መድረክ የተገኙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከሁሉም ክልሎች በተሰሩ ስራዎች ላይ የቀረቡ ሪፖርቶችን በሚገባ በመመልከት ፣ የመስክ ስራዎችን በግንባር በማየት እና በመገምገም የቀ

በኢትዮጵያ የውሃና ሳኒቴሽን ባለድርሻ አካላትን አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ ነወ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ ዩኒሴፍ በኢትዮጵያ ከአቅም ግንባታ ጋር በተያያዘ ለ18 ከተሞች ድጋፍ ማድረጉን እና ለሶስት ከተሞች ደግሞ በልዩ ሁኔታ አቅማቸውን የመገንባት ስራ እየሰራ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የጽዱ ኢትዮጵያን አላማ ለማሳካት በውሃ ሀብት ልማት ላይ እና በታዳሽ ኢነርጂ ሀብት ልማት ላይ እንደሚሰራ ተጠቆመ፡፡

የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባዘጋጀው ጽዱ ኢትዮጵ ንቅናቄ መድረክ ላይ የተገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ሡልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጽዱ ኢትዮጵያን አላማ ለማሳካት በውሃ ሀብት ልማት ላይ እና በታዳሽ ኢነርጂ ሀብት ልማት ላይ እንደሚሰራ ተጠቆመ፡፡

ከ82 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የተገነባው የመቆርቆር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል የሆነው በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን ሙህር አክሊል ወረዳ የመቆርቆር ንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በዘላቂነት አገልሎት እንዲሰጡ በየደረጃው ያሉ የውሃ ተቋማት ሚናቸው ከፍተኛ ነው ተባለ።

ውሃን ለማስተዳደር ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት ተቋማት ናቸው ያሉት ክብር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ፕሮጀክቶች ከተገነቡ በኋላ ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ እስከሚጠበቅባቸው የአገልሎት ዘመን እንዲደርሱ የተቋማት ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሄራዊ ኢነርጂ ኮምፓክት ረቂቅ ሰነድ ላይ ተወያየ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የስብሰባ ዋና አላማ በብሔራዊ ኢነርጂ ኮምፓክት ላይ በሁሉም ቁልፍ ባለድርሻ አካላት መካከል የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር በቀጣይ ሂደቱ ላይ በጋራ ርብርብ ለማድግ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡካን እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡካን እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዘርፉ አመራሮች በተገኙበት በፕሮጀክቶች አፈጻጸምና ቀጣይ ሊደረጉ በሚገባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል፡

ክቡር ሚኒስትሩ ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት በኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት በኢትዮጵያ ዳይሬክተር ሚ/ር ሉዊስ አንቶይን ሶሸ ጋር በውሃ ልማት ፈንድ በኩል እየተተገበረ በሚገኘው የባስኬት ፈንድ ፕሮግራም ላይ ትኩረት አድርጎ በተካሄደው ውይይት ሚ/ር ሉዊስ አንቶይን ሶሸ ፕሮግራሙን የበለጠ ውጤታማ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች

ትውልዱ ስለሀገራችን የውሃ ሀብት እንዲያውቅ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ፡፡

የዋን ላቭ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጂታል ኤግዚቢሽንን በጎበኙበት ወቅት ትውልዱ ስለሀገራችን የውሃ ሀብት እንዲያውቅ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በማሳካት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አስቻይ የውሃ እና የኢነርጂ ፖሊሲዎች ማዘጋጀት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃና ኢነርጂ ረቂቅ የፓሊሲ ሰነዶች ላይ በመከረበት መድረክ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን በማሳካት የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ አስቻይ የውሃ እና የኢነርጂ ፖሊሲዎች ማዘጋጀት ወሳኝ መሆኑ ገልጸዋል፡፡

May 2025

በውሃ እና ኢነርጂ ረቂቅ የፖሊሲ ሰነዶች ላይ ከባለድርሻ አካላት እና ከልማት አጋር ድርጅቶች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመጠጥ ውሃ እና ሳኒቴሽን፣ በኢነርጂ ልማት እንዲሁም የሁሉም የጀርባ አጥንት በሆነው የውሃ ሀብት አስተዳደር ላይ የነበረው ፓሊሲ የቆየ በመሆኑ አሁን ላይ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በላቀ ሁኔታ ለማረጋገጥ የተሻሻሉ ረቂቅ ፖሊሲዎች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ትውልዱ የውሃ ተመራማሪ፣ ተደራዳሪና ዲፕሎማት እንዲሆን በትምህርት ተቋማት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ መድረክ ላይ ትውልዱ ስለ ሀገሩ የውሃ ሀብት በሚገባ ተገንዝቦ ተመራማሪ፣ ተደራዳሪና ዲፕሎማት እንዲሆን በትምህርት ተቋማት ትኩረት በመስጠት አለምአቀፍ ተሞክሮን ለመቀመርና የውሃ ዲፕሎማሲያችንን ለማጠናከር በውሃው ዘርፍ የተሰማሩ ምሁራን፣ የምርምርና የሚዲያ ተቋማ

በመጪው የክረምት ወቅት በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች መደበኛና ከመደበኛ በላይ የዝናብ ሁኔታ እንደሚኖራቸው ተጠቆመ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ኢንስቲትዩቱ የተሰጠውን ተግባርና ሀላፊነት በተሻለ ብቃት ለመወጣት ከልማት አጋሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት በመስራት የማስፈፀም አቅሙን ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

12ኛው የውሃና የውሃ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በውይይት መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የውሃና ሀይድሮ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ ኢትዮጵያ በውሃ ሀብቶቿ ዙሪያ ከዚህ በፊት የተፈጠሩ ትርክቶችን ማረም እና እውነታውን ለአለም ለማሳወቅ የዘርፉ ሙሁራን ተሰባስበው አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ታሳቢ በማድረግ መጀመሩን ጠቁመዋል።

የአየር ሁኔታ ትንበያ በቀጠናው ሀገራት የድርቅና ጎርፍ ተጋላጭነትን ለመከላከል ጠቃሚ ነው ተባለ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከኢጋድ አባል ሀገራት ተወካዮች ጋር በነበራቸው ቆይታ በቀጣይ በቀጠናው ሊያጋጥም የሚችል የድርቅና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል መንግስታት ከቀረበው የሶስት ወር የቀጠናው የአየር ሁኔታ ትንበያ መነሻ አድርገው በመውስድ መፍትሄዎች ለማስቀመጥ እንደሚረዳቸው ተናግረዋል፡፡

ተግባር ተኮር ስልጠናው ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የመጠጥ ውሃ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ያግዛል ተባለ።

የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታምሩ ገደፋ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ ማድረግ እና የመጠጥ ውሃ ጥራት ስታንዳርድ ማዘጋጀት እንደሚገባ ገልጸው የውሃ የቢዝነስ ዕቅድ (Business plan) ሳይኖር የውሃ ታሪፍ መጨመርና መቀነስ አይቻልም የሚሉት አቶ ታምሩ መ

ክቡር ሚኒትሩ ከአለምባንክ ልኡካን ቡድን ጋር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ የመጠጥ ውሃ ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው፤ ከ76 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ ማድረግ መቻሉንና ሙሉ በሙሉ ለዜጎች ተደራሽ ለማድግ ከፍተኛ ጥረት እንደሚይቅ ጠቁመዋል፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አማካሪ ድርጅት የቅድመ ጥናት ሪፖርት ለውይይት ቀረበ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ኮርድኔተር ዶ/ር ከበደ ገርባ ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ሶስት አመት ማስቆጠሩን ገልጸው በከርሰ ምድር ውሃ ሀብት ልየታ፣ የመጠጥ ውሃ ግንባታ እና መስኖ ላይ ከፍተኛ በጀት ተበጅቶለት እየተተገበረ ያለ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡

ውሃን በአግባቡ በማስተዳደር ዘላቂ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃ ፕሮጀክት ስኬታማነት የሚለካው ፕሮጀክት በመገንባት ብቻ ሳይሆን የህብረተሰቡን ዘላቂና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ሲቻል ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን የውሃ አያያዝ ግንዛቤ በማሳደግ በታሪፍ ላይ የተመሠረተ ወቅታዊ የውሃ አገልግሎት ክፍያ መሰብሰብ

በኢነርጅ ዘርፍ የፖሊሲ ክለሳ መደረጉ የግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲጨምር የሚያስችል መሆኑ ተገለፀ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በማንኛውም አይነት የኢኮኖሚ ልማት አስተማማኝ ፣አዋጭ እና ቀጣይነት ያለው የኢነርጂ አቅርቦት ቅድሚያና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድ ውሃ ፕሮጀክት አተገባበር ላይ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና በመስኖና ቆላማ ሚኒስቴር በሚተገበረው የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድ ውሃ ፕሮጀክት ላይ ከአለም ባንክ በተውጣጡ ባለሙያች በፕሮጀክቱ አፈጻጸም ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚነስቴር የመጠጥ ዉሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ እና የፕሮክቱ አስተባባሪዎችና

የውሃ አገልግሎት ደህንነትን በማስጠበቅ ዘላቂ የውሃ አቅርቦትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

የመጠጥ ውሃ ተቋማት ክትትልና ድጋፍ ዴስክ ኃላፊ አቶ ሀይማኖት በለጠ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሁሉም ክልሎች በከተሞችና በገጠር መጠጥ ውሃ ተቋማት ላይ ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና በአፋር ክልል የከተሞች መጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመንና የበለጠ ተደራሽ ለማድረግ ብሎም የውሃ አገልግሎት ተቋማትን አቅም ማ

በ22 ወረዳዎች ያሉ መካከለኛ የውሃ ተቋማት አገልግሎታቸውን ዘላቂ ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፡፡

የመጠጥ ውሃ አቅርቦት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን በገጠርና በከተማ ተደራሽ ለማድረግ የGreen Climate Fund (GCF) ፕሮጀክትን በ 9 ክልልሎችና በድሬ ዳዋ ከተማ መስተዳድር ስር በሚገኙ 22 ወረዳዎች እየተተገበረ ነው ብለዋል፡፡