የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከደ/ኮሪያ ውኃ ኮፖሬሽን ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ።

የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከደ/ኮሪያ ውኃ ኮፖሬሽን ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ። የውኃና ኢነርጂ ሚንስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከኮሪያ ውኃ ኮርፖሬሽን ፕረዚደንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፓርክ ጄይ ጋር የትብብር ስምምነት በደ/ኮሪያ፣ ሲዎል ተፈራርመዋል። ፕረዚደንቱ በስምምነት ንግግራቸው የኢትዮጵያና ኮሪያ ግንኙነት እንደማንኛውም ሀገር የዲፕሎማሲና የልማት ትብብር ብቻ ሳይሆን በደም የታተመ መሆኑን አንስተው ኮርፖሬሽኑ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር በአጋርነት ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል። ክቡር ሚንስትሩ በበኩላቸው ፕረዚደንቱ ያነሱትን የሁለትዮሽ ግንኙነት አረጋግጠው ከድርጅቱ ጋር በውኃና ኢነርጂ ዘርፍ በቅርበት መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸውላቸዋል። የድርጅቱ ፕረዚደንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ በጥቅምት ወር 2015 ዓ/ም ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።

Share this Post