Dec 2025

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ ነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በያንጉዲ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እንሰራለን።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለደቡብ ሱዳን የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር ለመጡ ልዑካን የተዘጋጀው የልምድ ልውውጥ እና የአቅም ግንባታ ስልጠና ማጠቃለያ መርሀ ግብር ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ባደረጉት ንግግር ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እ

የዩኤን ዲፒ (UNDP)ስቲሪንግ ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይት አደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የዩኤንዲፒ/UNDP/አፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም እስቲሪንግ/String/ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች፣ በተዘረጉ አስቻይ ሁኔታዎች፣ በመጡ ለውጦችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይአድርጓል።

በጣም ገጠራማ ለሆኑ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሀይል ከሚያቀርቡ በዘርፍ ከተሰማሩ የ16 የግል ድርጅቶች ውል የማደስና ከ13 ተጨማሪ የግል ድርጅቶች ጋር ውል የመግባት ስነስርዓት ተካሄደ ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢትዮጵያ እምቅ የኢነርጂ ሀብት ያላት ሀገር እንደሆነና ከለውጡ ወዲህ እንደሀገር በዘርፉ ከፍተኛ ስራ ተሰርቶ ውጤት ምጣቱን ገልፀው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብና ቅንጅታዊ አሰራርን ይጠይቃል ብለዋል።

ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተገነባው የንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ውሃ ላይ ያሉ ትልቁ ስኬታችን ጉድጓድ ተቆፍሮ ውሃ ሲወጣ እና ፕሮጀክቱ ህይወት ዘርቶ ወደ ህብረተሰቡ ሲደርስ ነው በማለት የወረዳው ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከአጋር አካላት ጋር በጋራ መስራት የጎላ ሚና አለው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር Mr. Sune Krogstrup ጋር በከርሰምድር ውሃ ካርታ (ground water mapping) እና በአቅም ግንባታው ዘርፍ በትብብር ለመስራት በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃ ሀብት አስተዳደር ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የባዘርኔት ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል የቀላፎ ወረዳ አሎ አጋርሲ ተፋሰስ በተጎበኘበት ወቅት ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ከውሀ ሀብት እና ከመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበሩ ያሉ ስራዎችን ጎበኙ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ የውሀ ሀብት እና የመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካንን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋም የሆነውን የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንሰቲትዩት ፣የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የአቃቂ ፍሳሽ ማጣሪያ ማእከልንና የአዳማ ከተማ ውሃ አገልግሎትን ጎብኘተዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከስምንት አማካሪዎች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማስፋት በሚደረገው ጥረት እንደአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች ውስጥ በ55 ወረዳዎች በሚተገበሩ የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ስራዎች የአቅም ግንባታና ከግንባታ በኋላ የፕሮጀክቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ከአ

ለ22 ፕሮጀክቶች 26 እስታንድባይ ጀኔሬተሮች /standbygenerators/ የግዥ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት የሚገነቡ በአጠቃላይ በ55 ወረዳዎች 110 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንዳሉ ገልፀው ጀኔሬተሮቹ የሚገዛላቸው 22ቱ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙና በመጠናቀቅ ላይ የሉ ናቸው ብለዋል።

ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

የቪዥን አካዳሚ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጂታል ኤግዚቢሽኑን በጎበኙበት ወቅት ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

በሃዋሳ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት (Faecal Sludge and Septage Treatmenet Plant ) ግንባታና ጥገና የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ በ23 ከተሞች የሚተገበር የሁለተኛው የከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት አካል የሆነው በሃዋሳ ከተማ የሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ እና ማስወገጃ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከተሞችን ጽዱ፣ ማራኪ እና ውብ ለማድረግ እያከናወነ ያለ

ለሕዝባችን ሁለንተናዊ የውሃ አቅርቦትና የንፅህና አጠባበቅ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከገንዘብ ድጋፍ በላይ ውጤታማ አፈፃፀም በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ፒ..ኤች.ዲ) ባለፉት 3 ዓመታት የፕሮጀክቱን የአፈጻጸም ሂደት ለመገምገም እና በቀሪ ሦስት ዓመታት የፕሮጀክቱን ዓላማ ለማሳካት ለሚመጡት 3 ዓመታት የፕሮጀክት ትግበራ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መንግስትን እና ዓለም ባንክን የሚያጣምረው ይህ የግምገማ መድረክ ወሳኝ ምዕራፍ መሆ

በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ሲሉ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ''ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በተከበረበት ወቅት ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ብለዋል።

በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ ተግባራዊ ለሚደረገው የተቀናጀ ስራ ምቹ ሁኔታ መኖሩ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሰሞኑ በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ በባዘርኔት ፕሮጀክት ተግባራዊ የሚደረገውን የተቀናጀ ስራ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርትን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን ይህንን አስመልክቶ ለስራው የተመረጡ አካባቢዎች ተጎብኝተዋል።

ከ299 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የሲቪል ስራና የኤሌክትሮመካኒካል መስመር ዝርጋታ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የኢዋያ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቦረና አካባቢ እንደሚገኝ ገልፀው አካባቢው በከፍተኛ ሁኔታ ውሃ አጠርና ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በድርቅ የተጠቃ አካባቢ በመሆኑ ስራው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ በፍጥነትና በጥራት መሠራት አለበት ብለዋል።

ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ ቤቶች የቁሳቁስ የአቅም ግንባታ ድጋፍ ተደረገ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የቁሳቁስ ድጋፉ የተደረገው በ7 ክልሎች በ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ቤቶችን አቅም ለማጎልበት፣ አገልግሎቱን ለማዘመንና ለማሳለጥ እንደሚየግዝ ታስቦ ነው ብለዋል።

በ15 ሚሊዮን ብር የተቀናጀ የመረጃ ሲስተም ለማልማት ሶፍትዌር ከሚያለማ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃልማት ፈንድ ብድር አስተዳደር በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ደረጃውን በጠበቀ የመረጃ አያያዝ በአይቲ /Information Technology/ መደገፍና ሲስተሙ መዘርጋት ስላለበት የውልስምምነቱ አስፈልጓል ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ተግባር ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገለጹ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስና ለዘመናት የሀገር ዕድገት ማነቆ ሆኖ ቆይቷል፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ሰፊ ተግባር ውጤት መመዝገቡን ተናግረው ለዚህም ውጤት መመዝገብ በዋነኝነት የሚጠቀሠው የተቋማት አሠራር በሪፎርም እንዲቃኝ መደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት ተደረገ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ውሃን በተመለከተ በርካታ ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የውሃው ዘርፍ በራሱ ተደራጅቶ እንዲመራ መደረጉ ለውጤቱ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።

ከ48 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር የአቅም ግንባታ ስልጠና ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ በገጠርና በከተማ በተለያዩ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰራው የአቅም ግንባታ ስራ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለብዙ አመታት ያካበተውን አቅም በመጠቀም ብቃት ያላቸውን ባለሞያዎችን ለማፍራት ስት

Nov 2025

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ልማትፕሮጀክት የሩብ ዓመት የግምገማ ሪፖርት ቀረበ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ለማት ፕሮጀክት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች በተደጋጋሚ ከሚጠቁ አምስት የአፍሪካ አገራት የመጠጥ ውሃ እና መስኖ ልማት ዋነኛ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ አካባቢያዊ እና ማህበራዊ የል

የውሃ ሀብት አጠቃቀምንና ፈቀቃድ አሰጣጥን ማዘመን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክልል ውሃ ቢሮዎች፣ ከቤዚን አስተዳደር ፅ/ቤቶች፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤት እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች ተወክለው ከመጡ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የውሃ ሀብት አጠቃቀምና ፈቃድ አሰጣጥን ማዘመንና /E-Service/ አሰጣጥ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።

በክትትልና ግምገማ እና የመማማር ማዕቀፍ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፕሮጀክቶች ሳይት ዙሪያ ድጋፍና ክትትል በሚደረግበት ወቅት ኮንትራክተሮች ምን እንደሚሰሩ በጥልቀት መመርመር፣ አማካሪዎች ሚናቸውን በአግባቡ መወጣታቸውን መቃኘትና የመስሪያ ቤቱን አቅርቦት መፈተሽ ይገባል ያሉ ሲሆን እስከ ነሀሴ ወር መጨረሻ እያንዳንዱ ፕሮጀክት ያከናወናቸውን ተግባራት

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለው ለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጎበኘ።

በውሃ ልማት ፈንድ እያስገነባቸው ከሚገኙት የመካከለኛ ከተሞች መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እና ከ5000ሜትር ኩዩብ ውሃ የማጠራቀም አቅም ያለውን የለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ያስጎበኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች ፕሮጀክቶቹ በተሻለ

ከ839 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት አለኝታ ልየታና ልማት የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ፕሮጀክቱ የምስራቅ አፍሪካ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል ሲሆን በ240 ቀናት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ገልጸዋል፡፡

ወደ ሪፎርም መግባት ጊዜው የሚጠይቀው ተግባር መሆኑ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ሀገር በሁለተኛው ዙር ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት አንዱ መሆኑን የገለጹት አቶ ማሙሻ ሪፎርሙን በውጤታማነት ለመፈጸም በየደረጃው አብይ ፣ ቴክኒካል እና ንኡሳን ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ተግባር ተገብቶ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የድጅታል አሰራር ስርዓቱ የተለየ ተነሻሽነት ፈጥሯል ሲሉ የናይጄሪያ ቡድን አባላት ተናገሩ።

ባለሞያዎቹ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የመጡ ሲሆን በነበረው ውይይት በውሃ ሀብት አስተዳደር፣ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እና በኢነርጂ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከተለያዩ ለጋሽ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

ክቡር አምባሳደር በውይይቱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰረተ ልማት ግንባታ እና ዘለቄታዊ አገልግሎትን አስመልክቶ ከጤና፣ ከትምህርትና ከገንዘብ ሚኒስቴር መ/ቤቶች ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሆነ ገልፀው፤ በአሀዳዊ ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰ

ለሁለንተናዊ ጤና ውሃና የውሃ አስተዳደር ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

ከዓለም የውሃ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት /Internationale water management institute/፣ከጤና ሚኒስቴር እና ከሌሎችም ባለድርሻ ተቋማት ጋር በትብብር በተዘጋጀው መድረክ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ ውሃ ሀብት አስተዳደር ዋና ስራአስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ለሁለንተናዊ ጤና ውሃና የውሃ አስተ

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዘርኔት ፕሮጀክት የአቅም ግንባታ ስልጠና እያካሄደ ነው

የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ እንደገለጹት ስልጠናው በጂኦሎጂካል ኢንፎርሜሽን መረጃ ትንተናና በመሬት ቅኝት ዙሪያ የሃገራችንን ወሳኝ የሆነ ቴክኖሎጂ ለማስተዋወቅ የሚጀመርበት መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ከ202 ሺ ዪሮ በላይ በሆነ ወጪ የማማከር አገልግሎት የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ኢትዮጵያ ዘመናዊ አሰራርንና መረጃ አያያዝን ተግባራዊ እያደረገች ባለበት በዚህ ወቅት ከአሜሪካው አጎጊ ድርጅት ጋር የስራ ውል መግባቱ ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ገልፀው እድሉን ስላገኙ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የሱዳን አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር አል-ዘይን ኢብራሂምን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ በውይይታቸው ኢትዮጵያና ሱዳን የቆየ የሁለትዮሽ የግንኙነት ታሪክ እንዳላቸው ገልፀው፤ በሱዳን መንግስት በኩል በኢነርጂው ዘርፍ ከኃይል አቅርቦት ጋር ስላለው ግንኙነት አብራርተዋል፡፡

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የጋራ ግንዛቤ ሊኖር ይገባል ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በክቡር ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ሀይሌ ሪፎርሙን አስመልክተው ለተቋሙ ሰራተኞች ሰፊ ገለፃ እንደተሰጠ አስታውሰው፤ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በተቋማችን እንዴት መተግበር እንዳለበት የምናይበት ሰነድ ነው ብለዋል።

ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ የኢንዱስትሪ ፍሳሽ ቆሻሻን የማጣራትና መልሶ የመጠቀም የውሃ ጥራት መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂ ውጤታማ መሆኑ ተገለፀ።

አዲሱን ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ወደ ውሃ አካላት የሚለቀቀውን ፍሳሽ ተጣርቶ መለቀቁንም በየጊዜው በባለሞያዎች ክትትል ይደረጋል ያሉት አቶ መንበሩ፤ የቀይ ቡና መፈልፈያው ድርጅት የውጪ ምንዛሪ ከማስገኘቱም ባሻገር ለሴቶችና ወጣቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።

ከ 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ፕሮጀክቱ ትልቅ በመሆኑ በቁርጠኝነት ከውሃ አገልግሎት እና ከክልል ውሃ ቢሮዎች ጋር ሀብትን በአግባቡ መጠቀም ላይ ትኩረት በማድረግ እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡

በፈረንሳይ የአማካሪ ልማት ድርጅት በተጠናው የከተሞች ቅድመ መለያ መስፈርት እና የአዋጭነት የጥናት ሰነድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በማከል የውሃ ልማት ፈንድ ከተቋቋመበት አላማ በፖሊሲ ከተቀመጠው የከተሞች ኢኮኖሚማና ማህበራዊ ሀብት ውስጥ አንዱ እና ሰብአዊ መብትም ጭምር በሆነው ንጽህናው የተጠበቀ ውሃ ለህብረተሰቡ ማድረስ ሲሆን በዚህ ደግሞ በከተሞች አካባቢ ብርድ በመስጠት እንዲተገብሩት እየሰራ የሚገኝ ሲ

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምእራፍ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው፡፡

እንደ ሀገር ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት መካከል የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አንዱ ሲሆን ዘርፉ በኢኮኖሚያዊ ፣ በማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እድገት የሚጠበቁበትን ግቦች ለማሳካት የሰው ሀብት ትልቁን ድርሻ ስለሚይዝ ይህ ሀብት የሚመራበት ስርዓት በብቃት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የአገልግሎት አሰጣጡንም ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ

በክቡር ሚኒስትሩ የሚመራው ሉካን ቡድን የመስክ ምልከታ አካል የሆነውን የሰመራ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ያለበት ሁኔታ ምልከታ አደረገ;;

በውይይቱ ላይ ክቡር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ውስጥ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል።

ቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ /BaSRINET/ ፕሮጀክት የአዋሽ ቤዚን ፕሮጀክት ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የተፋሰስ ስራ የተጀመረው በአዋሽ ተፋሰስ ላይ እንደነበረና ተፋሰሱ ከዚህ በፊት በጎርፍ ምክንያት የዜጎች የመፈናቀልና የችግር መንስኤ ሆኖ መቆየቱን አውስተው አሁን ግን በፕሮጀክቱ በተሰሩ ስራዎች ለአካባቢው ህብረተሰብ እፎይታና የኢኮኖሚ ምንጭ መሆን ችሏል ብለዋል።

ጎርፍን ከስጋት ወደ በረከት መለወጥ እንደሚቻል ተገለፀ

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ በአፋርክልል በአሚበራና ዱለቻ ወረዳ ባደረጎት የሥራ ይፋዊ ጉብኝት በባለፉት ሁለት ዓመታት በአዋሽ ወንዝ ላይ በተሰሩ የ255 ኪሎ ሜትር የጎርፍ መከላከያና የወንዝ አመራር ስራዎች ጎርፍን ከስጋት ወደ በረከት መለወጥ እንደተቻለ ገልፀዋል፡፡

በሶላር ሚኒግሪድ ዝርጋታ ፣ጥገናና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሰለጠኑ ሰልጣኞች የብቃት ምስክር ወረቀት ተሠጠ።

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ኢትዮጵያ በሶላር ኢነርጂ የታደለች በመሆኗ ይህን ዕምቅ የሶላር ሀይል በበቂ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ሚኒስቴር የመስሪያ ቤቱ በዘርፉ የሚታየውን የብቃት ክፍተት በጥናት በመለየት ክፍተቱን ለመሙላት ስልጠናው ተዘጋጅቷል ብለዋል።

በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ዙሪያ የከርሰ ምድር ውሀ ሀብት አለኝታ ልየታና ልማት የሚውል የ11 የጉድጓድ ቁፋሮ ውል ተፈረመ

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ በተለያዩ ምክንያቶች መጓተት ካለ ለማህበረሰቡም ለኮንትራክተሩም አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው በማስገንዘብ፤ ችግሮች ካጋጠሙ በወቅቱ በመናበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲሚድረግ አረጋግጠዋል።

በሚኒግሪድ ሶላር ኢነርጂ አቅርቦት ለሚሰማሩ የግል አልሚዎች የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት እገዛ የሚያደርግ ስልጠና መመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ተሳታፊዎች ገለጹ

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አማካኝነት በሶላር ሚኒ ግሪድ ተከላ ስራ በሚሰሩ ስራዎች የግል አልሚዎችን ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የግል ባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት እንዲችሉ ለአስፈፃሚ አካላት በተሰጡት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ነው።

በዩኤንዲፒ ፕሮጀክት ለተመረጡ ባንኮችና ማይክሮፋይናንስ ተቋማት ስልጠና እየተሰጠ ነው

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ይመስላል ተፈራ እንደገለጹት የግልና የመንግስት ባንኮችና ማይክሮፋይናንስ ተቋማት በሚኒግሪድ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥና በፕሮጀክቱ በሚሰሩ የሶላር ሚኒግሪድ ትግበራዎች ለግል አልሚዎች የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ትብብር እንዲያደርጉ ነው ብለዋል፡፡

ከ611 ሚሊዬን ብር በላይ በሆነ አጠቃላይ ወጪ የመጠጥ ውሃ ግንባታና የውል አስተዳደር የማማከር ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ጨረታውን አሸንፈው የውል ስምምነቱን የፈረሙት ድርጅቶች ከሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ከዚህም በፊት የተለያዩ የማማከርና የግንባታ ስራዎችን በውጤታማነት ሰርተው ማስረከባቸውን አውስተው አሁንም የክልሉን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ በፍጥነትና በጥራት በመስራት

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የፕሮጀክት ግንባታ ለማከናወን ተስማማ

ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ፤ የድሬዳዋን ህዝብ በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ዮት ኮንስትራክሽን በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ስራውን አጠናቅቆ እንዲያስረክብ አሳስበዋል፡፡