የኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ውሃ ጥናት እና የውሃ ጉዶጓድ ቁፋሮና ግንባታ መመሪያዎች ለባለድርሻ አካላት ቀርበው ግምገማ ተካሄደባቸው።
ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አስቀድመው በከርሰ ምድር የውሃ ሃብት ዘርፍ በስራ ላይ የቆዩ፣ሲሰሩ የነበሩና አሁንም ስራውን በመምራት ላይ የሚገኙት ሙያተኞች እስከአሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነው ይህ ተግባርም አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ያለ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል።