የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሠራተኞች ለሕልውና ዘመቻው ስኬታማነት ላበረከቱት ዘመን የማይሽረው አስተዋጽኦ ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከአማራ ብሔራዊ ክልል የክብር ሽልማት ተበረከተለት፡፡ የክብር ሽልማቱን ክቡር ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እጅ ተቀብለዋል፡፡
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቀደም ብሎም በመከላከያ ሚኒስቴር 6ኛ ዕዝ ጠቅላይ መመሪያ በዘመቻው ለነበረው አስተዋጽኦ የዋንጫና የሰርተፍኬት ሽልማት አግኝቷል፡፡